በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ

ተለያዩ የኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ መንግሥት በምዕራብ ኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ መካከል ያሉትን ችግሮች እንዲፈታ ጠይቀዋል።

የኦሮሚያ ክልል ፀጥታ እና አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ ትላንት ከአሜሪካ ድምፅ የኦሮምኛ ክፍል ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ ችግሩን ለመፍታት በሁለቱ ወገን ውይይት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።