የኢትዮጵያውያንን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ውይይት በለንደን

የሀገር ጉዳይ ይመለከተናል ያሉ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሳምንቱ መጨረሻ በለንደን በተካሄደ ስብሰባ ላይ ተሳትፈው ተወያዩ። የውይይቱን መድረክ በለንደን ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውኢትዮጵያ ለአዎንታዊ ለውጥ በሚል የተመሰረተ አካል ነው።

የትናንቱ ስብሰባ ኢትዮጵያ አሁን በጀመረችው የለውጥ ሂደት ውስጥ ለሚታዩ ተግዳሮቶች ምላሽ የሚሆኑ ሀሳቦችን የመለዋወጥ ዓለማ ነበረው። ኤምባሲው በሀገሪቱ ለሚደረገው ለውጥ እና እንዲገኝ ለሚፈለገው እድገት ሁሉም የበኩሉን አስተዋፅዖ ለማበርከት የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዝ ገልጿል።