ቅዳሜና እሁድ 48 ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል፡፡

በሣምንቱ ማብቂያ 48 ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ውድድሮቻቸውን በበላይነት ማጠናቀቅ ችለዋል

በሣምንቱ ማብቂያ ቅዳሜና እሁድ በአለም ላይ በርከት ያሉ የግል የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድሮች ሲካሄዱ ሰንብተዋል፡፡ በዚህም ከወትሮው በተለየ 48 ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ውድድሮቻቸውን በበላይነት ለማጠናቀቅ ድል ቀንቷቸዋል፡፡ የዚህ ሣምንት ማብቂያ ውጤቶች ከምንጊዜው በላይ የኢትዮጵያውያን አትሌቶች የበላይነት የተመዘገበበት ሆኗል፡፡

በፍራንክፈርቱ ማራቶን 7 ተፎካካሪዎች ከ2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ በታች የገቡ ሲሆን ከነዚህ መካከል 6ቱ ኢትዮጵያውን ናቸው፡፡ ይህ ውድድር ጠናካራ ፉክክር የታየበትም ነበር፡፡ በጁብልጃና ማራቶን የተካፈለው አትሌት ሲሳይ ለማም በቦታው 2፡04.58 የሆነ አዲስ ሰዓት ማስመዝገብ ችሏል፡፡

የአትሌቶቹን ዝርዝር ውጤት ከታች ይመልከቱ፡-

ማራቶን

ፍራንክፈርት ማራቶን – ጀርመን

ወንዶች:
1. ከልክሌ ገዛኸኝ 2:06:37,
7. አሰፋ ተፈራ 2:08:34,
8. ፅዳት አበጀ 2:09:39,
11. ወርቅነህ ስዩም 2:12:55,

ሴቶች:
1. መስከረም አሰፋ 2:20:36,
2. ሃፍታምነሽ ተስፋይ 2:20:47,
3. በዳቱ ሂርጳ 2:21:32,
4. በላይነሽ ኦልጅራ 2:21:53,
5. ደራ ዲዳ 2:22:39,
6. ስንታዬሁ ለወጠኝ 2:22:45,
10. አበበች አፈወርቅ 2:25:17,
11. ማሬ ዲባባ 2:25:24,
12. ወርቅነሽ አለሙ 2:26:50,

ጁብልጃን ማራቶን – ስሎቬኒያ

ወንዶች:
1. ሲሳይ ለማ 2:04:58,
2. ገ/ጻድቅ አብርሃ 2:08:36,
4. አየለ አብሽሮ 2:09:12,

ሴቶች:
3. ድባቤ ኩማ 2:23:34,

ሬኔስ ማራቶን – ፈረንሳይ

ወንዶች:
2. ጫላ ደቻሳ 2:09:15,
5. ብርሃኑ ተሸመ 2:09:54,
7. ታደሰ አሰፋ 2:21:09

ሴቶች:
1. አልማዝ ነገደ 2:29:40,
3. አየሉ አበበ 2:34:13

ቾሰኒልቦ ማራቶን ቹንቺዮን – ኮርያ

ወንዶች:
1. ሺፈራው ታምሩ 2:08:50,
2. አዱኛ ቢቂላ 2:11:27,

ካዛብላንካ ማራቶን – ሞሮኮ

ወንዶች:
4. ኡርጌሳ ከድር 2:13:36,

ሴቶች:
3. ታደለች በቀለ 2:39:59,

ቨኒስ ማራቶን – ኢጣልያ

ወንዶች:
1. መኳንንት አየነው 2:13:23,

ሴቶች:
2. ሶሮሜ ነጋህ አመንቴ 2:38:59,

ደብሊን ማራቶን – አየርላንድ

ወንዶች:
1. አሰፋ በቀለ 2:13:23,

ሴቶች:
1. መሰራ ዱቢሶ 2:33:48,
2. ሞቱ ገደፋ 2:34:22

ግማሽ ማራቶን

ቫሌንሺያ ግ/ማራቶን – ስፔን

ወንዶች:
2. ጀማል ይመር 58:33,
3. አባዲ ሃዲስ 58:44,
4. አንዷምላክ በልሁ 59:19,
12. ተሸመ መኮንን 1:00:02,
23. ፍቃዱ ሃፍቱ 1:01:53,

ሴቶች:
1. ገለቴ ቡርቃ 1:06:11,
6. በቀለች ጉደታ 1:07:48,
7. የሺ ካልአዩ 1:07:58,
8. ሔለን በቀለ 1:08:39,

ሎዛን ግ/ማራቶን – ስዊዘርላንድ

ወንዶች:
1. ወዳጆ አለማዬሁ 1:06:57

ሴቶች:
1. ገለቱ እስራኤል 1:15:44

20 ኪ.ሜ. ማርሴል-ካሲስ ፈረንሳይ

ወንዶች:
1. አዱኛ ኦሊቃ 1:00:29,
2. አበራ ኩማ 1:00:30,
5. አየነው ይስማው 1:00:50,

ሴቶች:
1. ጌጤ አለማዬሁ 1:08:46,

ኮኬሊ 10 ኪ.ሜ – ቱርክ

ወንዶች:
2. ጌታዬ ገላው 29:36,

ሴቶች:
1. መስከረም ሰይፉ 33:27,

ምንጭ፡- የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን