በቡኖ በደሌ ደዴሳ ወረዳ ያሉ ዜጎች ከጥቅምት 10/2011 ዓም ጀምሮ ቤታቸው ሲቃጠል ሰንብቷል። ከትናንት ማታ ጀምሮ ጥቃቱ ስለተጠናከረና ቤታቸውም ስለተቃጠለ ሶስት ቀበሌ ውስጥ የሚኖሩ በርካታ ዜጎች ተፈናቅለዋል።
በአሁኑ ወቅት በቡርቃ ጃለላ ቀበሌ ሜዳላይ ዳስ ሰርተው ይገኛሉ። ከተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተፈናቅለው ባህርዳር የነበሩ ዜጎች ወደ ቦታቸው እንዲመለሱ መደረጉን የአማራ ብዙሃን መገናኛ ኤጀንሲ በቅርቡ መዘገቡ ይታወሳል። ተፈናቅለው የነበሩት ወደ ቀያቸው ተመለሱ እየተባለ እንደአዲስ ዜጎች እየተፈናቀሉ ነው።