ታዋቂዋ ኢትዮ-አሜሪካዊት የትግራይ ተወላጅ የሲቢኤስ ጋዜጠኛ ሔርሜላ አረጋዊ በትዊተር ገጿ ባሰፈረችው ጽሑፍ
–
የህወሓት ቡደን ደጋፊዎች ለትግራይ ህዝብ “ ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲደርሳቸው አይፈልጉም፤
ምክንያቱም እርዳታው ከደረሰ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) መንግሥት ጥሩ ሆኖ ስለሚታይና ፍላጎታቸው ስለማሳካላቸው ነው፣
የህወሓት ቡድን የትግራይን ህዝብ ለግል ፍላጎቱና ለሥልጣን ፍላጎቱ እየተጠቀመበት ነው፣
(1/3) My perspective on Tigray evolved bc of inconsistencies I’ve seen & heard in 10+ mnths. I stayed quiet for mnths hoping to see a shift towards peace & truth bc lives of millions – including my families’ – depend on it. There was no such shift. #Ethiopia
— hermela aregawi (@HermelaTV) September 19, 2021
በዲያስፖራው ማህበረሰብ በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ቢሰበሰብም ገንዘቡ የት እንደደረሰ አይታወቅም፣ ጦርነቱን ለመደገፍ እየዋለ እንደሆነም ትጠይቃለች፣
የህወሓት ቡድን በከፈተው ጦርነት በርካታ ንጹሃን ዜጎች እንደተገደሉ አይተናል፣
የትግራይ ተወላጅ ዲያስፖራዎች አሸባሪውን የህወሓት ቡድን በጭፍን ከደመደገፍ ታቅበው ቆም ብለው ማሰብ አለባቸው፣
–