የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በደብረ ማርቆስ በሚገኘው የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሌጅ ያሰለጠናቸውን ምልምል ልዩ ሀይል ፖሊስ አባላትንና እጩ የፖሊስ መኮንኖችን አስመረቀ።
በስነስርአቱ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር፣ የሰላምና የህዝብ ደህንነት ቢሮ ሀላፊው አቶ ሰማ ጥሩነህ እንዲሁም የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተኮላ አይፎክሩ ተገኝተዋል። (EBC)