የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በመስቀል አደባባይ የሚካሄደውን የኢፍጥር ፕሮግራም ተቃወመች። ቤተክርስቲያኒቷ በዓላቱ እንደተለመደው በእስታዲየም ውስጥ ማካሔድ እንደሚቻል ጠቅሳ ተከባብሮና ተቻችሎ የነበረውን የሃይማኖት ተከታዮችን የሚያቃቅር ሆኖ የሁከት መነሻ እንዳይሆን አስጠንቅቃለች።