የአለም ምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቤዝሌይ በትግራይ ያለው የሰብአዊ ድጋፍ መሻሻሉን አስታወቁ።ዋና ዳይሬክተሩ ዛሬ በትዊተር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት እንደገለጹት፤ በትግራይ ተገኝተው ከድርጅቱ ሰራተኞች ጋር ተወያይተዋል። በዚህም በክልሉ የሚደረገው ድጋፍ እየተሻሻለ መምጣቱን ተረድተዋል። እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለጻ፤ በሰብአዊ ድጋፉ ላይ መሻሻሎች ያሉ ቢሆንም ቀሪ ስራዎች አሉ። የዓለም የምግብ ፕሮግራም በክለሉ የተጠናከረ ስራ ለማከናወን ተጨማሪ ገንዘብ እንደሚያስፈልገውም ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።
–
I’m back on the ground here in #Ethiopia, talking with our team, getting updates and continuing to push to reach everyone in need in #Tigray. Important progress being made, but much more to do. We need $107 million ASAP to scale-up @WFP‘s operations. pic.twitter.com/HOqensXjug
— David Beasley (@WFPChief) February 25, 2021