የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።

–
ይህ ታሪካዊ መኖሪያ ሲፈርስ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር እና ባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ እንዲሁም ራሱ የቅርስና ጥበቃ ባለሥልጣን አያውቀውም።
–
ኢትዮጵያ የቅርስና ጥበቃ ባለሥልጣን ም/ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው፤ “ቅዳሜ እለት ወደ ውስጥ ዘልቀን በመግባት ለማስቆም ስንሞክር በወታደሮች እንዳንገባ ተከልክለን ተመልሰናል” በማለት ለሸገር ራዲዮ ተናግረዋል።
–
ቦታውን በባለቤትነት ለመያዝ የተዘጋጀው የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ እንደሆነና ስፍራውን ለኦሮሚያ ፖሊስ ልዮ ኃይል ካምፕ ግንባታ እፈልገዋለሁ ማለቱን የጠቆሙት ፕሮፌሰር አበባው፤ በአሁን ሰዐት ሙሉ ለሙሉ ፍርስራሹን አውጥተው በመጣል ታሪካዊውን ቅርስ ጠራርገው እንደደፉት አረጋግጠዋል።
–

–
ካልጠፋ ቦታ የተመዘገቡ ቅርሶች ያሉባቸውን መካናት እያሰሱ ማፍረስ አውቀውትም ይሁን ሳያውቁ ይማንነት አሽራ ድምሰሳ ተግባር በመሆኑ አጥብቅን እናወግዘዋለን::
–
በባህል በቅርስ ጥበቃ እና በቱሪዝም ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቶች የተመደቡ እነ ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌውን እና ሠርጸ ፍሬስብሐትን የመሰሉ ባለሙያዎች ጮኸው የማይሰሙ ተቆጥተው የማያስቆሙ ከሆነ ታዲያ ለማን አቤት ይባላል? – Yohannes Mekonnen