የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ፌዴራል መንግስቱንና ሕወሓትን የሚያደራድሩ ሶስት የቀድሞ የአፍሪካ መሪዎችን ሾሙ ተባለ

The primary task of the Special Envoys is to engage all sides to the conflict with a view to ending hostilities, creating conditions for an inclusive national dialogue to resolve all issues that led to the conflict, and restoring peace and stability to Ethiopia. AU Special Envoys: Ellen Johnson-Sirleaf, former President of the Republic of Liberia; Joaquim Chissano, former President of the Republic of Mozambique; Kgalema Motlanthe, former President of the Republic of South Africa – Addis Standard
DW : የኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥት እና ህወሓትን ለማሸማገል የቀድሞዋ የላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍን ጨምሮ የሶስት አገራት የቀድሞ መሪዎች ወደ አዲስ አበባ ሊጓዙ ነው። የአፍሪካ ኅብረት የአመቱ ሊቀ-መንበር የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ለሽምግልናው የመረጧቸውን ልዩ ልዑካን ዛሬ ይፋ አድርገዋል።
ከጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. ዕኩለ ለሊት ገደማ ጀምሮ ውጊያ የገጠሙትን የኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥት እና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይን ለማሸማገል የአፍሪካ ኅብረት ልዩ ልዑካን ሆነው ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙ ሶስት መሪዎች መምረጣቸውን ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ዛሬ ይፋ አድርገዋል።
ፕሬዝዳንቱ ውሳኔያቸውን ይፋ ያደረጉት የጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ ልዩ ልዑክ ሆነው ወደ ደቡብ አፍሪካ ካቀኑት ርዕሠ-ብሔር ሣህለ ወርቅ ዘውዴ ከተገናኙ በኋላ ነው።
በዚህም መሠረት የቀድሞዋ የላይቤሪያ ፕሬዝዳንት ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ፣ የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ክጋሌማ ሞትላንቴ እና የቀድሞው የሞዛምቢክ ፕሬዝዳንት ዮአኪም ቺሳኖ በኅብረቱ ሊቀ-መንበር አሸማጋይ ሆነው ተመርጠዋል።
ፕሬዝዳንት ራማፎሳ እንዳሉት “ልዑካኑ በኢትዮጵያ ግጭት ውስጥ የገቡ ወገኖችን ለማሸማገል” በመጪዎቹ ቀናት ወደ አዲስ አበባ ይጓዛሉ። ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድም ሽምግልናውን ተቀብለዋል።
“የልዩ መልዕክተኞቹ ተቀዳሚ ተግባር ጠብን ለማስቆም በግጭቱ የሚሳተፉ ሁሉንም ወገኖች ማወያየት፤ ወደ ግጭት ለመሩ ጉዳዮች መፍትሔ ለማበጀት ለአካታች ብሔራዊ ውይይት ሁኔታዎችን መፍጠር እና ለኢትዮጵያ ሰላም እና መረጋጋት መመለስ ነው” ሲሉ ከፍ ያለ ኃላፊነት እንደተጣለባቸው ራማፎሳ ጠቁመዋል።
“በትግራይ እና በኢትዮጵያ ጦር መካከል ስላለው ግጭት” ከርዕሠ-ብሔር ሣህለ ወርቅ ማብራሪያ የቀረበላቸው የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ራማፎሳ “በኢትዮጵያ ግጭት በመቀስቀሱ እጅግ እንዳሳሰባቸው” ለርዕሠ-ብሔር ሣህለ ወርቅ ገልጸዋል። “ግጭቱ በተሳታፊ ወገኖች መካከል በሚደረግ ውይይት ማብቂያ እንዲበጅለት ያላቸውን ጥልቅ መሻት” ለርዕሰ-ብሔሯ አሳውቀዋል።

The current African Union Chair and South African President Cyril Ramaphosa has appointed three African “distinguished Statespersons”: Joaquim Chissano, former President of the Republic of Mozambique; Ellen Johnson-Sirleaf, former President of the Republic of Liberia; Kgalema Motlanthe, former President of the Republic of South Africa – as Special Envoys of the African Union to help to mediate between “the parties to conflict” in Ethiopia, a statement released by the office of the AU Chairperson said.

The statement was released after talks between President Sahle-Work Zewde and South African President Cyril Ramaphosa.

President Sahle-Work traveled to South Africa today in “her capacity as Special Envoy of Prime Minister Abiy Ahmed.”

President Ramaphosa has expressed his gratitude to His Excellency Prime Minister Abiy Ahmed for accepting this initiative, and affirming the cooperation of the Ethiopian government in facilitating the work of the Special Envoys.

AU Chairperson and South African President Cyril Ramaphosa

The fighting between the Ethiopian federal armed forces and the Tigrayan armed forces started on November 04 after PM Abiy gave order to federal forces to start offensive against TPLF in Tigray after he said the TPLF “took measures” and “tried to rob the Northern Command,” based in Mekelle, the capital. He also accused TPLF “opened war through Dashlah.”

addis standard