ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በዋሽንግተን ዲሲ ለኢትዮጵያው ባደረጉት ንግግር ያነሷቸው ነጥቦች
•የኢትዮጵያዊነትን ህብር ቀለም ስላሳያችሁን አመሰግናለሁ
• የጋራ ዕራይ መሰነቅ ለዛም መሰለፍ ለዓለም ያስመሰከራችሁ በመሆናችሁ ግርምት ፈጥራችኋል
• ኢትዮጵያዊነት ከደማችን ጋር የተዋሀደ መሆኑን ዋሽንግተን ምስክር ናት
• ለ40 ዓመታት የገነባነው ከፋፋይና የጥላቻ ግንብ ለማፍረስ ዛሬ ቃል እንግባ
• ስንደመር የኢትዮጵያን ቀን የምናውጅ መሆናችንን ዛሬ አይተናል
• ግንቡን ማፍረስ ብቻ በቂ አይደለም ስለዚህ ግንቡን እዳፈረስን ድልድዩን እንገንባ
• የሚገነባው ድልድይ ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ለትውልድም ጭምር ሊሆን ይገባል
• እኛ ኢትዮጵያውያን እንደ አደዋ ዛሬም ታሪክ እንሰራለን
• ኢትዮጵያዊነት ተፈትሎ የተሸመነበት ድርና ማግ ስንርቅ የሚበጠስ በለአንድ ቀለም ነጠላ ሳይሆን አውታረ ብዙ ረቂቅ ጥበብ ነው
• በይቅርታ ዛሬ እንደመር
• ከመቶ ሚሊየን በላይ ኢትዮጵያውያን ስንደመር አንድ ቢሊየን አፍሪካን እንመራለን
• ያልተሰጠን የለም ምንም እንደሌለን ያደረገን በጋራ አለመምራቸን ነው
• ኢንጂነር ስመኘውን መግደል እንጂ የህዳሴ ግድብን ማቆም አይቻልም