ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በዋሽንግተን ዲሲ ለኢትዮጵያው ባደረጉት ንግግር ያነሷቸው ነጥቦች

ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በዋሽንግተን ዲሲ ለኢትዮጵያው ባደረጉት ንግግር ያነሷቸው ነጥቦች

•የኢትዮጵያዊነትን ህብር ቀለም ስላሳያችሁን አመሰግናለሁ

• የጋራ ዕራይ መሰነቅ ለዛም መሰለፍ ለዓለም ያስመሰከራችሁ በመሆናችሁ ግርምት ፈጥራችኋል

• ኢትዮጵያዊነት ከደማችን ጋር የተዋሀደ መሆኑን ዋሽንግተን ምስክር ናት

• ለ40 ዓመታት የገነባነው ከፋፋይና የጥላቻ ግንብ ለማፍረስ ዛሬ ቃል እንግባ

• ስንደመር የኢትዮጵያን ቀን የምናውጅ መሆናችንን ዛሬ አይተናል

• ግንቡን ማፍረስ ብቻ በቂ አይደለም ስለዚህ ግንቡን እዳፈረስን ድልድዩን እንገንባ

• የሚገነባው ድልድይ ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ለትውልድም ጭምር ሊሆን ይገባል

• እኛ ኢትዮጵያውያን እንደ አደዋ ዛሬም ታሪክ እንሰራለን

• ኢትዮጵያዊነት ተፈትሎ የተሸመነበት ድርና ማግ ስንርቅ የሚበጠስ በለአንድ ቀለም ነጠላ ሳይሆን አውታረ ብዙ ረቂቅ ጥበብ ነው

• በይቅርታ ዛሬ እንደመር

• ከመቶ ሚሊየን በላይ ኢትዮጵያውያን ስንደመር አንድ ቢሊየን አፍሪካን እንመራለን

• ያልተሰጠን የለም ምንም እንደሌለን ያደረገን በጋራ አለመምራቸን ነው

• ኢንጂነር ስመኘውን መግደል እንጂ የህዳሴ ግድብን ማቆም አይቻልም