በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞንና በደቡብ ክልል ጌዲኦ ዞን ካለፈው ሚያዝያ ወር አንስቶ በተቀሰቀሱ ግጭቶች ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር 970 ሺህ ያህል መድረሱን አለማቀፉ የስደተኞች ድርጅት ትናንት ባወጣው መረጃ አስታውቋል፡፡በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በተከሰቱ ግጭቶች ከደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ክልል ጌዲኦ ዞን 822 ሺህ 187፣ ከኦሮምያ ክልል ጉጂ ዞን ደግሞ 147 ሺህ 40 ሰዎች መፈናቀላቸውን …