አዲሱ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ለሐምሌ 6 በጎንደር ሕዝባዊ ስብሰባ ጠራ።

ታላቅ የህዝባዊ ሥብሠባ ጥሪ
……….
የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) የመጀመሪያውን ህዝባዊ ሥብሠባ በአማራ ተጋድሎ አብሳሪዋ የታሪክ ቋት ጎንደር ከተማ ሐምሌ 6 ቀን 2010 ያካሂዳል።

በሥብሠባው የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አመራሮች ከህዝቡ ጋር ይፋዊ ውይይት ያካሂዳሉ፣ የህዝባችን ጥያቄዎች ይነሳሉ፣ የመፍትሄ አካሄዶች ይጠቆማሉ። በእለቱ በቦታው ተገኝታችሁ አጋርነታችሁን ታሳዩ ዘንድ ተጋብዛችኋል።
ቦታ፦ ጎንደር ሲኒማ አዳራሽ
ሠዓት፦ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ