«ታሪኩን የሰዉ ልጅ መስማት አለበት» ዋቱ ዋቴ

አዉቶቡስ ዉስጥ የገቡት የአሸባብ ታጣቂዎች የክርስትና እምነት ተከታዮች የሆኑ ተጓዦችን ነጥለዉ አዉጥተዉ ለመግደል ሲጥሩ፤ አዉቶቡስ ዉስጥ አብረዉ ሲጓዙ የነበሩ የእስልምና እምነት ተከታዮች ጣልቃ ገብተዉ አፈሙዝ የተደገነባቸዉን ክርስትያን ተጓዦች ሕይወት ለማትረፍ ያደረጉት ፍልምያን የሚያስታዉስ ነዉ።