በኢትዮጵያ ቫይረሱ ከተገኘባቸው 365 ሰዎች ውስጥ 228 የሚሆኑት በአዲስ አበባ እንደሚገኙ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
–
የልደታ ክ/ከተማ 40 በመቶ የሚሆነውን ቫይረሱ ያለባቸውን ሰዎች ቁጥር ሲይዝ አዲስ ከተማ ክፍለከተማ በሁለተኛነት ድርሻውን መያዙን ዶ/ር ሊያ ታደሰ ገልጸዋል፡፡
–
ይህም ቫይረሱ በአዲስ አበባ በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መምጣቱን የሚያመላክት እንደሆነ ነው የተገለጸው፡፡
–
የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የሌላቸው እንዲሁም ቫይረሱ ካለበት ሰው ጋር ግንኙነት ሳይኖራቸው በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 16 በመቶ መድረሱንም ዶ/ር ሊያ አስታውቀዋል፡፡
–
የቫይሱን ስርጭት ለመቆጣጠርም ከቫይረሱ ጋር ንክኪ ያላቸውን ሰዎች ቅኝት የማድረግ ስራ ዋነኛ ተግባር መሆኑን የገለጹት ደግሞ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት ዳይሬክተር ዶ/ር ኤባ አባተ ናቸው፡፡
–
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 በተደረገ ቅኝት ከቫይረሱ ጋር ንክኪ ከነበረው አንድ ሰው ጋር ንክኪ የነበራቸው 32 ግለሰቦች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል፡፡
–
በተመሳሳይ በወረዳው በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ በተደረገ ድንገተኛ ምርመራ 40 የህግ ታራሚዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል፡፡
–
የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ እስካሁን 62 ሺህ 300 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን ካለፉት 2 ወራት ይበልጥ በ2ሳምንት ውስጥ የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር 63 በመቶ ድርሻ እንዳለው ገልጸዋል፡፡
–