የአዲስ አበባና የኦሮሚያ ፖሊስ ቤተክርስቲያናትን በመዳፈር የኢትዮጵያን ባንድራ በማውረድ ላይ ነው
ካዛንችስ አዲስ አበባ በሚገኘው በደብረ ፅጌ ቅዱስ ኡራኤል ቤተክርስቲያን የተሰቀለውን ባንዲራ የአዲስ አበባና የኦሮሚያ ፖሊስ አውርዱ በማለቱ የኡራኤልና የአካባቢው ህዝብ በቆራጥነት አናወርድም የሚመጣውን አብረን እናያለን በማለት መፋጠጣቸውን ለመረጃ ኮም የደረሰው መረጃ ያመላክታል::
እንዲሁም አራት ኪሎ በሚገኘው ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን በመግባት ተሰቅሎ የነበረውን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የአዲስ አበባና የኦሮሚያ ፖሊስ ወርሮ በኃይል አውርዶታል።የአፍሪካ ኅብረት ቅዱስ ሚካኤል ወጣቶች የአደባባዩን ሣር ታበላሻላችሁ በሚል ፖሊሥ ሊከለክላቸው ቢሞክርም ወጣቶቹ በሕግ አምላክ እንዳትጠጉን “ የኦነግ ባንዲራ ሲተከል የት ነበራችሁ? ” በሚል ተጨቃጭቀዋል። በኋላም የመከላከያ ፓትሮል የያዙ ወታደሮች መጥተው ፖሊሶቹን ተውአቸው ብለው በማለፋቸው አሁን በወታደሮቹ በመከላከያ ሠራዊቱ ትእዛዝ ወጣቶቹ በሠላም አደባባዩን በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በማስዋብ ላይ ይገኛሉ።