የሕወሓት ሰላዮችና የሶማሌ ልዩ ሓይሎች አዲስ አበባ ሊያደርጉት የነበረ አፈና ከሸፈ።

የሕወሓት ሰላዮችና የሶማሌ ልዩ ሓይሎች አዲስ አበባ ሊያደርጉት የነበረ አፈና ከሸፈ።

የቀደሞው የኢፌዴሪ ተወካዮች ምክር ቤት የሶማሌ ክልል ተወካይ የነበሩትን የሶማሌ ክልል መሪ አብድ እሌይ አገዛዝ ተቀዋሚ የሆነውን አቶ አሊ ገአን ዛሬ ምሽት ላይ በአዲስ አበባ ከተማ በቦሌ ሚከኤል በአራን ሆቴል የታጠቁ የትግራይ ደሕንነቶችና የአብዲ ኢሌይ ልዩ ሐይሎች አፍናው ወደ ጂግጂግ ለመውስድ ያደረጉት ሙከራ በቦታው የነበሩ ዜጎች ባደረጉት ርብርብ የፌዴራል ፓሊስ ጥረት ሊከሽፍ ችሏል ። አቶ አሊ በአሁኑ ስአት ወረዳ 17 ፓሊስ ጣቢያ እንደሚገኙ አረጋግጥናል ።

ባለፈው ሳምንት ከሚኒሶታ የመጡ አንድ የክልሉ ተወላጅን ለማፈን የተደረገ ጥረት መክሸፉ ይታወሳል።