አሜሪካ ሳንዲያጎ ግዛት በተካሄደ የግማሽ ማራቶን ውድድር መሰረት ደፋር በሴቶች አንደኛ ሆና ስታሸንፍ በወንዶች ፈይሳ ለሊሳ ሁለተኛ በመሆን አጠናቋል፡፡መሰረት በሳንዲያጎ የተደረገውን የማራቶን ውድድር ለማጠናቀቅ የፈጀባት ጊዜ 1 ሰዓት ከ8 ደቂቃ ከ27 ሰከንድ ነው፡፡
በውድድሩ ኬንያዊትዋ ጄን ኬቢ ሁለተኛ በመሆን መሰረትን ተከትላ ገብታለች፡፡
በወንዶች በተደረገው የግማሽ ማራቶን ውድድር ቱቱስ ኢኩሪ አንደኛ በመሆን ሲያሸንፍ ፈይሳ ሌሊሳ ሁለተኛ በመሆን አጠናቋል፡፡