ኤልያስ ስሜ የስሚዝሶኒያን የአፍሪካ የሥነ-ጥበብ ሽልማት ተሸላሚ ሆነ

በዩናይትድ ስቴትስ ዋሺንግተን ዲሲ የሚገኘው ስሚዝሶኒያን ብሄራዊ የአፍሪካ ጥበብ ቤተ-መዘክር ፥ ለአራተኛ ጊዜ አፍሪካዊ የስነ-ጥበብ ባለሙያዎችን የክብር ሽልማት አበርክቷል።የዘንድሮዎቹ ተሸለሚዎች ኢትዮጵያዊው የህብረ-ጥበባት ባለሙያ ኤልያስ ስሜ እና ናይጄሪያዎ የዕይታ ጥበብ ባለሙያ ኒጂዲካ አኩኒዬ ክሮስቢ ናቸው። በስፍራው ተገኝተን ያየነውን በቀጣዩ የምስል ዘገባ እናስቃኛችኋለን።