በለንደን የኦርቶዶክስ አማኞች በቤተክርስቲያን ላይ የሚሰራው ደባ ይቁም ሲሉ ሰላማዊ ሰልፍ ወጡ

አትድከሙ ክርስቲያን ተስፋ አይቆርጥም – ለንደን/እንግሊዝ

ዘመድኩን በቀለ

በእንግሊዝ ከማንችስተር፣ ከሊድስ፣ ከኒውካስትል፣ ሀርድርስ ፊልድና ካርዲፍ የተዋሕዶ ልጆች ወደ ለንደን እየገቡ ነው። የለንደን ዝናብ እኚኚኚኚ ቢልም እነሱ እቴ ሰልፉ ሳይጀመር ዝማሬያቸውን እያፈሰሱት ነው።

ልጆቿ በለንደን መሰባሰብ ጀምረዋል።

Image may contain: 1 person, wedding, crowd and outdoor

• በታላቋ፣ በጥንታዊቷና በብሔራዊቷ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚደርሰውን ሁለንተናዊ መንግሥታዊ በደል ለመላው ዓለም ህዝብ የማሳወቅ ዘመቻ አካል የሆነ የተዋሕዶ ልጆች ሰልፍ አሁን ሊጀመር ነው።

Image may contain: 11 people, people on stage, crowd, child and outdoor

• ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ወደ ለንደን እየተመሙ ነው።
• ድንኳን እየተጣለ ነው።
• አሁን በዚህ ሰዓት ለንደን ዝናባማ ብትሆንም የተዋሕዶ ልጆች እንኳን ዝናብ እሳት ለምን አይዘንብም በማለት ለእናት ቤተ ክርስቲያን ያላቸውን ፍቅር ለመግለጽ ተዘጋጅተዋል።

★ የአውሮጳ ዝናብ የሙከጡሪ ዓይነት ዝናብ አይምሰልህ፣ ጥርስ አለው። አኝ ነው የሚያደርግህ። አያ ጅቦ ነው። የእጅ እግር ጣት የሚያቃጥል እንደ እሳት ያለ ጠባይ ያለው ነው። ይሄን ተቋቁሞ ደጅ መዋል በራሱ ሰማዕትነት ነው።

Image may contain: one or more people, people standing, shoes and outdoor
መዝሙር 137 ከ ቁ 1-7 በለንደን ጎዳኖዎች ይጸለያል።
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በባቢሎን ወንዞች አጠገብ በዚያ ተቀመጥን፤ ጽዮንንም ባሰብናት ጊዜ አለቀስን።
² በአኻያ ዛፎችዋ ላይ መሰንቆቻችንን ሰቀልን።
³ የማረኩን በዚያ የዝማሬን ቃል ፈለጉብን፥ የወሰዱንም፦ የጽዮንን ዝማሬ ዘምሩልን አሉን።
⁴ የእግዚአብሔርን ዝማሬ በባዕድ ምድር እንዴት እንዘምራለን?
⁵ ተዋሕዶ ሆይ፥ ብረሳሽ፥ ቀኜ ትርሳኝ።
⁶ ባላስብሽ፥ ምላሴ በጕሮሮዬ ይጣበቅ፤ ከደስታዬ ሁሉ በላይ ኢየሩሳሌምን ባልወድድ።
⁷ አቤቱ፥ በኢትዮጵያ ቀን የኤዶምን ልጆች አስብ፦ እስከ መሠረትዋ ድረስ አፍርሱ አፍርሱ ያሉአትን።
⁸ አንቺ ወራዳ የባቢሎን ልጅ ሆይ፥ ስለ ተበቀልሽን የሚበቀልሽ የተመሰገነ ነው።
⁹ ሕፃናቶችሽን ይዞ በዓለት ላይ የሚፈጠፍጣቸው የተመሰገነ ነው።

•••

ሻሎም ! ሰላም !

Source — ዘመድኩን በቀለ