በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር ስር የሚገኙና በኦዲት ግኝት ጉድለት የተገኘባቸው እና ለከተማዋ ዋና ኦዲተር መስርያ ቤት ምላሽ ያልሰጡ 53 ተቋማት በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ውሳኔ ተላለፈ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ም/ቤት እያካሄደ ባለው መደበኛ ጉባኤ በከተማ አስተዳደሩ ስር የሚገኙ እነዚህ ተቋማት በከተማው ዋና ኦዲተር መ/ቤት እና ምክር ቤት በፀደቀው ዓዋጅ መሠረት በተሰጣቸው ጊዜ ውስጥ በኦዲት ግኝቱ ላይ ምላሽ እንዲሰጡ ቢጠየቁም በወቅቱ ምላሽ ለመስጠት ስላልቻሉ ተቋማቱ በህግ እንዲጠየቁ በሙሉ ድምፅ ወስኗል፡፡
እነዚህ ከ2008-2010 ዓ.ም ምላሽ ያልሰጡ 53 ተቋማት በዋና ኦዲተር መ/ቤት ና በከተማው ም/ቤት በሚደነግገው መሠረት ምላሽ እንዲሰጡ የሁለት ወር የጊዜ ገደብ ቢሰጣቸውም ምላሽ እንዳልሰጡ ታውቋል፡፡
ምንጭ:- የከንቲባ ፅ/ቤት