250 የሚሆኑ የጎንደር ዩንቨርስቲ የህክምና ሳይንስ ኢንተርን ተማሪዎች ግቢውን ለቀው አንዲወጡ ተደረገ።

ቁጥራቸው 250 የሚሆኑ የጎንደር ዩንቨርስቲ የህክምና ሳይንስ ኢንተርን ተማሪዎች ግቢውን ለቀው አንዲወጡ ተደረገ።የጎንደር ዩንቨርስቲ የህክምና ሳይንስ ኢንተርን ተማሪዎቹ እንደሚናገሩት ዩኒቨርስቲው በሆስፒታሉ ላይ ስላሉ ችግሮች ያነሳነውን ጥያቄ በ15 ቀን ውስጥ እመልሳለሁ ካለ በኃላ መልስ ስንጠብቅ ግቢውን ለቀን እንድንወጣ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ሰማን ግቢውን ለቀን ወጥተናል ይላሉ።