አዲስ ወግ የመቻቻልና የመከባበር ውይይትና የንግግር ባሕል መድረክ ዛሬም እንደቀጠለ ነው

አዲስ ወግ የመቻቻልና የመከባበር ውይይትና የንግግር ባሕል መድረክ ዛሬም እንደቀጠለ ነው

ያለፈውን 1 ዓመት በኢትዮጵያ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖሊቲካዊ የለውጥ ሂደትን የሚቃኘው አዲስ ወግ መድረክ የ2ኛ ቀን ውይይት እንደቀጠለ ነው።

አዲስ ወግ የመቻቻልና የመከባበር ውይይትና የንግግር ባሕልን የሚያስተዋውቅ መድረክ ነው።

መጋቢት 14 ቀን 2011 ጠዋት እየተደረጉ ባለው ውይይት አቶ ደሳለኝ ራሕማቶ፣ ዶ/ር ሰዒድ ኑሩ፣ አቶ ኢየሱስ ወርቅ ዛፉና ወ/ሮ ብርሃኔ አሰፋ የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት፤ የምጣኔ ሀብት ዕድገት፣ ሥራ ፈጠራና ማኅበራዊ አካታችነት ዙሪያ በግብርና ምርታማነት፣ የጥቅል ኢኮኖሚው ሚዛን መዛባትና የዕዳ ጫና ላይ በስፋት እየተወያዩ ነው።

ምንጭ፡-ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት