ኢትዮጵያ ሙስና አለቅጥ ከተንሰራፋባቸዉ ሀገራት አንዷ ናት – ጀርመን ራዲዮ
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
በዚሕ ሳምንት አንድ አድማጫችን ከኢትዮጵያ በላኩልን የSMS መልዕክት «ኢትዮጵያ ዉስጥ ሙስና እንደ አንድ የሥራ-መስክ እየተሰራበት ነዉ»፥-በማለት የሙስናን ወይም የንቅዘትን መንሠራፋት ባልተወሳሰበ አማርኛ ገልፀዉት ነበር። በአድማጫችን አስተያየት የማይስማሙ በርግጥ ይኖራሉ። ትራንስፓረንሲ እንተርናሽናልን የመሳሰሉ ጉዳዩን ያጠኑ ድርጅቶችና ባለሙያዎች እንደሚሉት ግን ኢትዮጵያ ባጭር ጊዜ ዉስጥ ሙስና በተለይ የባለሥልጣናት ሙስና አለቅጥ ከተንሰራፋባቸዉ ሐገራት አንዷ ናት። ዛሬ ደግሞ አዲስ አበባ ዉስጥ በኢትዮጵያ ሥለላዉ ሙስናና ደረጃዉ የተደረገ ጥናት አዲስ አበባ ዉስጥ ይፋ ሆኗል። ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ ዝርዝር ዘገባ አለዉ።