ጥቃታችን ከፋና እኛንም አስከፋን


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


ከገረመው አራጋው

ሀገራችን ኢትዮጰያ በአሁኑ ሰአት እጅግ በከፋ ሥራ አጥነት፣እየጨመረ የሄደ የእኩልነት ፍትህ መታጣትና: ሥር የሰደደ ድህነት በከፍተኝ ሁኔታ አለመረጋጋት ፈጥሮባታል ለዚህም ዋነኝ ተጥያቂ መለስና ግብረአበሮቹ ናቸው::  ከአንደበታቸው የስድብ ቃላትን በማዝነብ ለዘለዓለም የበላይ ሆነው የሚኖሩ የመስላቸው እነዚህ አምባገነን; ፋሽስታዊው; በዘርና; በትንሽ መንደር የተደራጀው የወያኔ ቡድን ላለፉት 21 አመታት በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ በጉልበት: እጅግ በጣም ሁዋላ ቀርና የህዝብን ጥቅም ይማያስጠብቅ የአገዛዝ ስርአት በመጫን የስልጣን ዕድሜውን ማራዘም; የአገር የማፈራረስና የኢትዮጵያዊንትን ታሪክና ባህልን የማጥፋትና ተልኮውን መፈጸም እና የህዝብና የሀገር ሀብት መዝረፋን መጠነ ሰፊ በሆነ ሁኔታ እየፈጸም ይገኛል::ህዝቡን በጥመንጃና በአራዊት ህግ በማስፈራራትና ከታች የተዘረዘሩትን ተፈጥሮዊና ህገመንግስታዊ መብቶችን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በመከልከል የባንዳንትና የሌብነት ተግባሩን በመፈፅም ላይ ይገኛል::

የወያኔ የሞኝ እድሜ ማራዘሚያው እስትራቴጂ ህዝቦችን በዘር  በብሄር በቋንቋ  በሀይማኖት በቀለም  ብሎም በጎጥ እንዲለያዩ ማድረግና ክፍተኛ የጥላቻ ፖለቲካ ቅስቀሳ በህዝቡ ዘንድ ማሰረጨት:: እርስ በእርስ እንዳይስማሙ: አብረው እንዳይኖሩ  አንድንት እንዳይፈጥሩ  በህብረት ማህበራዊና ፖለቲካዊና እኮኖሚያዊ ችግሮቹን በጋራ እንዳይፈቱ የሀገር ውስጥና የውጭ ጥላቶቹን ለመታገል አቅምና ስምምነት እንዳያጎለብቱ በዘር ፖለቲካ እንዲወጠሩ ማድረግ  ከእያንዳንዱ ብሄረሰብና ሀይማኖቶች ለሆዳቸው ያደሩትን ጥቂት ግለሰቦችን ቆንጥሮ እምነትህ ተጥብቆልሀል ባህልህ ጥቅምህ ተከብሮልሀል ብሎ በህዝብ ላይ መሳለቅ::

ወያኔ እራሱ በማያከብረው ይህን  ከአርቃቂዎቹ በስተቀር ለአብዛኛው ሕዝብ ግልፅ ያልሆኑ ብዙ ነገሮች ያሉበት ሕገ-መንግሥት  የህጎች ሁሉ የበላይ ብሎ በሚጥራው ህገ መንግስቱ ላይ የተፃፉትን  ህጎች ለተወሰኑ ግለሰቦችና ቡድኖች ብቻ ስንዲሰራ ማድረግ በርካታ የህዝብን ተፈጥሮዊና ህገመንግስታዊ መብቶችን  መናገር  የመፃፍ  የመሰብሰብ በቡድን የመደራጀት ሀሳብን በአደባባይ ወጥቶ የምግለፅ: በሀገሩ ላይ የመሬት ባለቤት መሆን  የፈለገውን እምነት መከተልና የመሳሰሉትን በኢትዮጵያ ተፈፃሚ እንዳይሆኑ ማድረግ ወይንም በመሸራረፍና ለጥቂት የወያኔ አባላትና ደጋፊዎች ብቻ ተፈፃሚ እንዲሆን ማድረግ::

በኢትዮጰያ ውስጥ የወያኔን የተሳሳተና ከገደብ ያለፈ የጭቆና   አገዛዝ በአደባባይ መቃወም  ስለ ኢትዮጵያዊነት መደራጀት መስበክ መናገርና ማዜም መጻፍ እንደወንጀል የሚቆጥርበት ጊዜ ላይ ተደርሳል:: ሆኖም በአሁን ሰአት ወያኔ መጥነ ሰፊ ዘመቻ እያደረገ ያልው ታዋቂና ለወደፊት ለአምባገነኑና ለፋሽስቱ ለወያኔ ቡድን የስልጣን ቆይታ አደገኛ ሊሆኑ ይችላሉ ብሎ የሚያስባቸውንና በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነትና ታማኝነት ያላቸውንና አላቸው ብሎ የሚጠረጥራቸውን የተቃዋሚ የፖለቲካ መሪዎችን  አባላቶችን  ደጋፊዎችን  ምሁሮችን  መምህራኖችን  ጋዜጠኞችን  ዘፋኞችን  ነፃ አሳቢ ዜጎችንና በተለያዩ የዲሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ ላይ የሚሳተፉ ግለሰቦችን ማስፈራራት:በእስር ማሰቃየት  በአካላቸውና በስነልቦናቸው ላይ ጉዳት ማድረስ:ንብረታቸውን መውረስ መዝረፍ ማውደም  አስፈራርቶ ከሀገር እንዲሰደዱ ማድርግ: የት እንደደረሱ እንዳይታወቅ ማድረግ  መግደልና ሌሎችንም የመሳሰሉ ወንጀሎችን በመፈፅም ሀገር የማፈራረስ ህዝብንና ሀገርን የማዋረድና የባንዳነት ተልኮውን መወጣት::

ለህዝብ ዲሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ በጣም አስፈላጊ የሆኑ ለምሳሌ በሰባዊ መብት:በመልካም አስተዳደር:በህግ የበላይነትና የመሳሰሉ ጉዳዮች ላይ መጥነኛም ሆነ ጥልቅ ግንዛቤ እንዳያገኝና እንዳይኖረው ተግተው በመስራት ህዝቡ በዲሞክራሲያዊ ስርአቱ ግንባታ ላይ ምንም አይነት ተሳትፎ እንዳይኖረው ማድረግ:: ስለ ሰባዊ መብት መልካም አስተዳደር የህግ የበላይነትን ለህዝቡ በማስተማርና በማስረፅ ላይ የተሰማሩትን መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች: ነፃ ጋዜጦች: የራዲዮና የቴሌ ፕሮግራሞችን ሆን ብሎ የተለያዩ አፋኝና ሰንካላ ሰላማዊዮቹንና የብዙሀኑን መብት የሚያቀጭጩ የሌቦችንና የጥቂቶችን ቡድኖችን ስልጣን የሚያፋፋ ህጎችንና መመሪያዎችን አውጥቶ ለህዝቡ እንዳይደርሱ ማድርግ:: ህዝቡም መብቶቹን እንዳያውቅና እንዳይጠቅም ማድረግ::

ለውጭ ሀገርዜጎችና ለጥቂት የወያኔ ቡድን አባላት መሬት የማግኘት ያልተገደበ መብት በተሰጠባት ሃገር በገዛ ሃገራቸው ከአንድ ክልል ወደሌላ ክልል በመሄድ  መኖር የጀመሩ ወገኖችን ክልላችሁ ስላይደለ ወደክልላቸው ተመለሱ መባላቸው የወያኔ አገር የማፈራረስ ተልኮው ገሀድ ወጥቶበታል ::የኢትዮጵያን ህዝብ የሀገር የመሬትና የንብረት አልባ አድርጎ የወያኔ አባላት ብቻ የመሬትና የንብረት ባለቤት እንዲሆኑ ማድርግ:: ሀገርንና መሬትን ለባእዳን መሸጥና ለጎረቤት ሀገሮችም ትላልቅ መሬቶችን ቆርሶ በመስጥትን በመሸጥ አሳልፎ መስጠት; እኛ ብቅርጽና በመጠን የምናውቃትን ታሪካዊ ኢትዮጵያን ማጥፋት; ህዝቡም በሀገሩ ላይ ስለ መሬት እንዳይጥይቅ በጠመንጃ ማስፈራራት; ምንም እንደማያመጣ በጥጋብና በስድብ ንቀቱን መግለፅ::

የኢትዮጵያን የ3000 አመት ታሪክ መካድ: አሳፋሪ በሆነ መልኩ ማቅረብ: ታሪክን መበረዝ: የፈጠራ ታሪክ መፍጠር:: የኢትዮጵያን ህዝብ ባህል: ስብእና  ዕምነት  ኩራት  ማንነት  ብሄራዊ እሴቱን  አንድነቱንና ብሄራዊ መገለጫዎቹን ማጥፋት:: የኢትዮጵያን ታራክ የወያኔን ታሪክ ብቻ አድርጎ በካድሬዎቹና ለሆዳቸው ባደሩ ተራ ግለሰቦች ገንዘብ ከፍሎ ማፃፍ ለምሳሌ የአድዋ ጦርነትን ያሸነፉት ኢትዮጵያውያን ሳይሆኑ፣ትግሬዎች ናቸው  ብሎ የሀገርንና የኢትዮጰያን ታሪክ መካድ :: ልክ እንደ ውጭ ጠላቶቻችን ኢትዮጵያዊነትን ማዋረድ  ማጥላላት  ማናናቅና የመሳሰሉትን አስነዋሪ የቅጥረኝነቱን ተግባር እየፈፅመ ይገኛል::

የኢትዮጵያን ምንም አይንትአማራጭ የመረጃ ምንጭ እንዳያግኝ ማድረግ:: የኢትዮጵያ ህዝብ ትክክለኛ እውነተኛና ሚዛናዊ መረጃዎችን እንዳያገኝና በኢኮኖሚ: በማህበራዊ: በፖለቲካ: በዲሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ ላይ ቀጥተኛ ተሳታፊ እንዳይሆን ማድረግ:: እኔ አውቅልሀለው የምነግርህን ብቻ ተቀበል ብሎ ህዝብን በወያኔ የመረጃ ማሰራጫዎቹ ማደንቆር:: ትክክለኛ እውነተኛና ሚዛናዊ መረጃዎችን ለህዝቡ የሚያደርሱትን የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር የመረጃ ተቃማትን የግል ጋዜጣዎችን ራዲዮዎች ቴሌቪዥን እና ድህረ ገዕች መረጃዎችን ለህዝቡ እንዳያደርሱ ለማድረግ አታሚ ድርጅቶችን መዝጋት  ፈቃድ መከልከል  ባለቤቶቹን ማስፈራራት ማሰር: በቁጥር እጅግ ብዙ የሆኑ ጋዜጥኝች የታሪክ ፅሀፊዎች ተኪነጥበብ ሰዎች ከሀገር እንዲሰደዱ ማድረግ:: በራዲዮና የቴሌቢጅን የሚሰራጩትን መረጃዎች ከፍተኛ ገንዘብ በማውጥት ሞገዳቸውን ማፈን::

የመለስና የግብራበሮቹ አደባባይ የወጣው የቅጥፈት ተግባራቸው በይስሙላ ምርጫ አጭበርብሮም ሆነ በመሳሪያ አስገድዶ ስልጣን መጨበጥ፣ ስልጣን  ላይ መቆየት፣ ሃብት ማጋበስ፣ ርዕዩተ ዓለማቸውን ተጠቅመው ህበረተሰቡን ስልጣን ላይ እንዲያቆያቸው አድርገው ማዋቀር ፣ ነፃ ሲቪክ  ድርጅቶች እንዳይኖሩ ወይንም እንዲዳከሙ ማድረግ፣ ነፃ ፕሬስ እንዳይኖር ያሉትም ተዳክመው እራሳቸውን  ሳንሱር ማድረግ እንዲለምዱ፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በሚመለከት ደግሞ የተወሰኑትን በገንዘብ ድጎማ ወይንም በፍራቻ ተለጣፊዎቹ እንዲሆኑ ማድረግ ሲሆን ጠንካራ  እና ሃቀኛ በሆኑት ተቃዋሚዎች ላይ ደግሞ የፖለቲካ   እና የገንዘብ ምህዳሩ እንዲጠብባቸው እና እንደልባቸው እንዳይንቀሳቀሱ በማድረግ ተዳክመው የኢትዮጵያን  ህዝብ  የመንግስት ስልጣን ባለቤት ለማድረግ ከጀመሩት ሰላማዊ እና ህገ መንግስታዊ ትግል ሜዳ እንዲወጡ ለማድረግ ያልተቋረጠ ጫና ማድረግ ናቸው።

አሁን የተፈጥረው የትግል እንቅስቃሴ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ  ህዝብ  እንዚህን ሁሉ ግፍና በደሎች እያደረሱበት ያሉትን ጥቂት የግለሰብና ቡድኖች ስብስቦችን ከፍተኛ በሆነ የቁጭትና በጀግንንት ወኔ ከሁሉም አቅጣጫ በድርጅትም ተሰብስቦ ሆነ በተናጥል በመሆን የተፈጥሮአዊና ሰብአዊ መብቶቹን ለማስከበር ያላሰለሰ ትግል እያካሄደ ይገኝል:: የኃይማኖት ተቋማት፣ ሰራዊት፣ ፖሊስ፣ ወጣቶች፣ ምሁራን፣ ሴቶች፣ አርሶአደሩ፣ ከተሜው፣ ሰራተኛው፣ ስራ አጡ፣ ነጋዴው፣ ባለሀብቱ እና የመሳሰሉትን የህብረተሰብ ክፍሎች  በማሳተፍ ከትግሉ የሚጥበቀውን ውጥት በአጭር ግዜ ለማምጥት ሁሉንም የትግል ስልቶች በመጥቀም  ሀገራችንን ከአምባገነኖች መዳፍ ለማውጥት በአንድነት መታገል አማራጭ የሌለው ውሳኔ ሊሆን ይገባል::