ወያኔ ተጨናንቆአል?


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


ርግጥ ነው ሰሞኑን ወያኔ በጣም ተጨናንቆአል።

ለአመፅ እርሾ ሊሆኑ በሚችሉ ቁጣዎች ተከበዋል። የሶማሊያ ተልእኮ እየከሸፈ ነው። አልሸባብ እያሸመቀ ደጋግሞ አደጋ መጣሉን በመቀጠሉ፣ ከዚህ በላይ ሶማሊያ መቆየት እንደማይችሉ ተረድተው ጓዛቸውን መሸከፍ ይዘዋል። ከኤርትራ ጋር የጀመሩት የጦርነት ድራማ፣ ላይ ላዩን ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ እንደሚያውሉት አለመሆኑ ተባኖበታል። የውስጥ ቀውሱ ተባብሶአል። የመምህራን አመፅ ወዴት እንደሚያመራ አልታወቀም። ቢታፈንም መልኩን ቀይሮ መከሰቱ የማይቀር ነው። የኦርቶዶክስ ቤተክርስትያንን ነባር ቅርሶች የማውደሙ ሴራ አማኙን ህዝብ ያሸማቀቀና ያስደነገጠ ሆኖአል። ገና አልተቋጨም። ከደቡብ ክልል የተፈናቀሉት አማሮች ጉዳይ፣ ሊታፈን ባለመቻሉ ፈንድቶ ወጥቶአል። የኑሮ ውድነቱና የዋጋ ግሽበቱንም ሊቆጣጠሩት አልቻሉም። ሙስናው ጣራ ነክቶአል። ስርቆቱ፣ “ተከተል አለቃህን” የሚል ስያሜ አጊኝቷል። የህወሃት ወገኖች የቅንጦት ህይወት ይሉኝታ አጥቶአል። እና በዙሪያቸው ያለውን የተቆጣ የህዝብ አይን ለማፈን መጨነቃቸውን ማስተዋል ይቻላል። አፈና ግን መፍትሄ ሊሆን አይችልም።

ምርጫው አንድ ብቻ ነው። ከራስ ጋር እና ከእውነታው ጋር መታረቅ!

(“የቅዳሜ ማስታወሻ” እስከ ትናንት ኢትዮጵያ ላይ ይጎበኝ ነበር። ዛሬ ማለዳ ስመለከት ግን “ኢትዮጵያ” በሚለው ስር ምንም አያሳይም። በፌስቡክ በኩል የኢትዮጵያ አንባቢዎቼን ጠይቄ፣ ከዛሬ ማለዳ ጀምሮ የእኔና የአቤ ቶክቻው ብሎጎች መዘጋታቸውን አረጋግጠውልኛል። በርግጥ ደብረፅዮን ብሎግ እያሳደደ መዝጋት ከጀመረ ስራ በዝቶበታል ማለት ነው።)