የትግሬ ወያኔ ቡድን የአርማጭሆን አብድራፊ የምትባል ከተማ ለመውሰድ እያሰፈሰፈ ነው::
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
የትግሬ ወያኔ ቡድን ወልቃይትን : ጠገዴን : ጠለምትን እና ሁመራን ከጎንደር በመውሰድ ሳያቆም አሁን ደሞ በራሱ ህገ መንግስት የአማራ ክልል ነው ያለውን ቦታ ለመውሰድ እያሰፈሰፈ ነው::
ነገሩ እንዲህ ነው:: በሰሜን ጎንደር ዞን የምእራብ አርማጭሆ ወረዳ የምትገኝ #አብድራፊ የምትባል ከተማ አለች::
ከተማዋ ከዛሬ አምስት አመት በፊት #የምእራብ_አርማጭሆ ወረዳ ዋና ከተማ ነበረች::
ከተማዋ ለሱዳን ቅርብ የሆነች እና በሰሊጥ ምርት የታወቀች ከተማ ናት::
ወያኔ ይችን ከተማ ለራሱ ለማድረግ ስለፈለገ ከዛሬ አምስት አመት በፊት የምእራብ አርማጭሆ ወረዳ ዋና ከተማ ለሱዳን ቅርብ የሆነችው አብድራፊ መሆኗ ቀርቶ ከሱዳን ወደ ጎንደር 25ኪሜ ገባ ብላ የምትገኘው #አብርሃ ጂራ የምትባለው ከተማ እንድትሆን ወስኗል::
ከዚህ ውሳኔ በኋላም የአብድራፊ ከተማ የበለጠ ወደ ትግራይ ኢንተግሬት እንድታደርግ ለማድረግ ከሁመራ እና ዳንሻ ወደ አብድራፊ የሚወስድ አስፓልት መንገድ ገንብቷል::
የአማራው ተውካይ ነኝ የሚለው ብአዴን ግን ከተማዋን ወደ መተማ እና ጎንደር ለማስተሳሰር መንገድ አልገነባላትም:: የአብድራፊ ከተማ አንገረብ እና አዲስ አለም የሚባሉ ሰፈሮች አሏት:: የከተማዋ ሃላፊ (ትግሬ) ከትግራይ ክልል ትግራዮችን እየጠራ አዲስ አለም በሚባለው ሰፈር ቦታ እየሰጣቸው ነው:: በአንጻሩ ከተማዋ የአማራ ክልልም ብትሆንም አማራወች ከተማዋ ላይ ቦታ የማግኝት እድላቸው ተዘግቷል::
አማራው ታግሎ ሁሉንም የተወሰዱበትን መሬት ካላስመለሰ በቀር የትግሬ ወያኔ ወረራ መቸም አያቆምም::