በባህርዳር ከተማ ከፍተኛ ተኩስ እየተሰማ ይገኛል::


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


እንደተፈራው በደብረማርቆስ ደመራ ላይ ሕወሓት ብጥብጥ አስነስታ ብዙ ወጣቶችን አሰረች – ስነ ሥርዓቱ ተቋረጠ – ባህርዳር ተኩስ ይሰማል
(ዘ-ሐበሻ) በደብረማርቆስ ከተማ በተደረገ የደመራ በዓል ላይ የሕወሓት መንግስት እንደተፈራው ብጥብጥ አስነስቶ በርካታ ወጣቶችን ማሰሩ ተሰማ::
የዘ-ሐበሻ የዜና ምንጮች ከስፍራው እንደዘገቡት ከሆነ በደብረማርቆስ ደመራ ላይ የሕወሓት መንግስት ሆን ብሎ ብጥብጥ እንዲነሳ በማድረግ ወጣቶችን ዳመራ በጠበጡ በሚል አስሯል:: እንዲሁም በርካታ ወጣቶች እንደተቀጠቀጡም የደረሱን መረጃዎች አመልክተዋል::
እንደ ምንጮቻችን ገለጻ የሕወሓት መንግስት የአማራውን ወጣት ለትግል ተነሳሽነቱን ለማኮላሸት በዚህ የደመራ ስነ ሥነስርዓት ላይ ባዘጋጃቸው ሰዎች ሆን ብሎ እንዲበጠበጥ አድርጓል:: ቀደም ብሎ ሕወሓት ይህን በማደረግ ወጣቶችን ለማሰር እንዳቀደ ዘ-ሐበሻ መዘገቧ አይዘነጋም::
ይህ በ እንዲህ እንዳለ በባህርዳር ከተማ ከፍተኛ ተኩስ እየተሰማ ይገኛል:: ተኩሱ እየተሰማ ያለው በባህር ዳር ቀበሌ 13 መኮድ አካባቢ ሲሆን ከፍተኛ ዝናብ እየጣለ እንደሚገኝም ታውቋል:: ዘ-ሐበሻ ተኩሱ ለምን እና እንዴት እንደተፈጠረ በማጣራት ላይ ናት::