የማለደ ወግ … ክበረ ነክ ፣ ጸያፍ ስድብ በመንግሥት ቴሌቪዥን ! [ነቢዩ ሲራክ ]
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
የማለደ ወግ … ክበረ ነክ ፣ ጸያፍ ስድብ በመንግሥት ቴሌቪዥን ! [ነቢዩ ሲራክ ]
ቴሌቪዥኑ ከዘባተሎ ፖለቲካ መረጃ ቅበላ ወደ ብሽሽቅ መድረክነት
በሰሜን አሜሪካ የሚኖሩው የኢትዮጵያ ሶማሌ ዲያስፖራዎች የወያኔ / ኢህአዴግን መንግሥት ደግፈው ፣ ግንቦት 7 እነ ኦነግን ተቃውመው ሰልፍ መውጣታቸውን ሰምተናል ። በዚሁ ሰልፍ ይዘውት የወጡት መፈክርን የያዘውን ክበረ ነክና ጸያፍ ስድብ ከትናንት ምሽት ጀምሮ በማህበራዊ ድረ ገጾችና በፊስ ቡክ ሲሰራጭ ተመልክተናል ። ምራቃቸውን የዋጡ አባቶች ፣ ወንድሞች ሂጃብ ያደረጉ የኢትዮ ሴቶች የተካተቱበት የድጋፍና ተቃውሞ ሰልፍ ይዘውት የወጡት” ኦነግ ተ… ዳ !” የሚለውን መፈክር ይገኝበታል ፣ ደጋግሜ አይቸው ማመን እቅቶኝም ነበር ። ወደ ኋላ ግን እርጠኝነቱን ስረዳ እዝነ ልቦና ያለው ያደርገዋል በማልለው ስድብ አዘል መፈክር ለእነሱ እኔ እስከ መሸማቀቅ ደርሻለሁ ፣ ያሳፍራል ፣ ያሳዝናል
ዛሬ እኩለ ቀን ደግሞ ክበረ ነክ ፣ ጸያፍ ስድቡ በመንግሥት ቴሌቪዥን ላይ ቀርቦ ስመለከተው ደግሞ ይበልጥ ተሸማቀቅኩ ፣ አዘንኩ የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን ተገቢ የልሆነ መረጃ ለመሰራጨቱ አዲስ ባይሆንም ” ኦነግ ተ… ዳ !” ብሎ የተጻፈን ነውረኛ መልዕክት በህዝቡ በሚደጎም ጣቢያ ማሳዬት ትልቁ የመንግሥት ተቋም ምን ያህል በዘቀጠ አስተደደር እንደሚመራ በገሃድ ያሳይ ይመስለኛል ።
በመንግሥት ቴሌቪዥን ይህን መሰል ጸያፍና ተገቢ ያልሆነ ተራና የወረደ የወሮበላ ስድብ ማስተናገዱ ያስቆጫል ። ይህም የመንግሥት ቴሌቪዥኑ ወደ ከተራ የተዛባ ዘባተሎ ፖለቲካ መረጃ ቅበላ ወደ ብሽሽቅ መድረክነት እየቀየረው መሆኑ በእርግጥም እንደ ዜጋ ያስቆጫል … በዚህች ሀገር የሰው ሰብአዊ መብት በጠመንጃ ሲጣስ ብቻ ሳይሆን ክብረ ነክ ጸያፍ የሚባል ነውር በአደባባይ ሲናኝ ” ተው ” ባይ ሽማግሌ ጠፍቶ እንዲህ መባዘናችን ልብ ይሰብራለረ ያማል
እስኪ ቸር ያሰማን !
ነቢዩ ሲራክ
እስኪ ቸር ያሰማን !
ነቢዩ ሲራክ