በዐማራ ሕዝብ የተጠራ የሥራ ማቆም አድማ የለም!
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
በዐማራ ሕዝብ የተጠራ የሥራ ማቆም አድማ የለም!
ከመስከረም 9 እስከ 14 ቀን 2009 ዓ.ም በሕዝባዊ እምቢተኛነት ኮሚቴ የቤት ውስጥ የሥራ ማቆም አድማ በባሕር ዳር እና በጎንደር ተጠርቷል እየተባለ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው ወሬ ከዕውነት የራቀ ምናልባትም ወያኔዎች ወጣቱን በየቤቱ ለማፈስ የዘየዱት ሊሆን እንደሚችል በባሕር ዳርና በጎንደር ዛሬ ያነጋገርናቸው ሰዎች ገልጸዋል።
በዚህ ሰዐት የቤት ውስጥ አድማ መጥራት ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል። ትግሉ ከፍተኛ ደረጃ በደረሰበት በዚህ ሰዐት የቤት ውስጥ አድማ መጥራት ትግሉን ወደ ኋላ የሚጎትት ይሆናል።
ይህ ጥሪ የዐማራ ሕዝብ የማያውቀው ሲሆን ወያኔዎች በመከላከያ ሠራዊት፣ በብሔራዊ ደኅንነትና በፌደራ ፖሊስ የሚመራ ወጣቶን ማደን በጀመረበት በዚህ ጊዜ የቤት ውስጥ አድማ ተጠርቷል መባሉ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ ተንኮል ወይም የኦፕሬሽኑ አካል ሊሆን እንደሚችል ተገልጿል።