አንድ ነገር ይገርመኛል – ኢህአዴግ ዘንድ ቀላል እና ከባድ ነገር እንኳን የሚለይ ሰው መጥፋቱ!


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


By Meski Ab Fits : የኮንሶ ህዝብ ጥያቄ በጣም ቀላል ነው :: እነዚህ ወገኖች የጠየቁት ‘ጉዳያችንን ለማስፈፀም የዞን ከተማ ፍለጋ እንደ ማጅላን ከምንዞር በአቅራቢያችን ማዕከሉን ያደረገ የዞን መዋቅር ኖሮን ፖለቲካዊ ጉዳያችንን በቅርብ እያስጨረስን እንኑር’ ነበር ። ገታራው መንግስት በዚህ መስማማቱን በጄ ስላላለ ደግሞ ‘እሽ የልዩ ወረዳ መዋቅራችንን እንኳን ይዘን እንቀጥል’ ሲሉ ለድርድር የተመቸ ሃሳብ ይዘው መጡ :: ይህም አይሆንም ባይ ነው ጀግናው ኢህአዴግ ! ይህ ነው ከሃያ ዘለግ ያሉ ኮንሶዎች እንዲሞቱ በቂ ሰበብ የሆነው ::


አንድ ነገር ይገርመኛል – ኢህአዴግ ዘንድ ቀላል እና ከባድ ነገር እንኳን የሚለይ ሰው መጥፋቱ!

ከወልቃይት እና የአዲስ አበባ ዙሪያ (የኦሮሚያ ) ጥያቄ አንፃር የኮንሶ ጥያቄ እጅግ ቀላል ነው :: ለምን ቢባል የኮንሶ ጥያቄ የሚያደናቅፈው ነገስታት እና ቤተ ዘመዶቻቸው የገተሩት ፎቅ የለም ፤ በኮንሶ “ዲሞቢላይዝድ” የሆነ ወታደር የሚንፈላሰስበት “ፕላንቴሽን” የለም ፣ በኮንሶ በደባልነት ገብቶ ባለቤት ሊያስወጣ የሚያምረው የመንግስት ቤተዘመድ ብዙ የለም ::

ነገሩን በአንፃራዊነት ለማሳየት እንጅ የእነ አጅሬ እግር ያልረገጠው ለምለም መሬት የለምና በኮንሶ የሉም ለማለት እንዳልሆነ ይሰመርበት ::  ኢህአዴግ ለቤተ ዘመዶቹ እግራቸው የረገጠውን ሁሉ የሚያወርስ የዘመድ አዝማድ መንግስት መሆኑ ሳይረሳ ኮንሶዎች የጠየቁት ጥያቄ ቢያንስ ዛሬ ለቤተዘመዳዊው መንግስት የቅርምት ስስ ብልቱንየሚመታ አይደለም:: በቅርምት ቀልድ ለማያውቁ ገዥዎችም የኮንሶ ጥያቄ እንደ ኦሮምያና ወልቃይት እጅግም አስበርጋጊ አይደለም ::

ኮንሶዎች የጠየቁት ለስልጤ ህዝብ ከተደረገው ቢያንስ እንጅ አይበዛም ፤ ለቅማንት እና ለአርጎባ ህዝብ ከተደረገው ልዩ ነገር ኮንሶ አላነሳም። ምን ቆርጧችሁ ትንፋሻችሁ ተሰማ ካልተባለ በቀር ! ‘ያለ አግባብ የትራንስፖርት አናውጣ ጉዳይ ይዘን የዞን ከተማ ፍለጋ አንንከራተት’ ማለት የአዲስ አበባውን ዙፋናችሁን አስረክቡን ማለት አይደለም ::እንደምንም አድርጌ ባስበው የኮንሶ ህዝብ ዞኑ ቢቀር የልዩ ወረዳ መዋቅር ይኑረን የሚል ጥያቄ የሚያስገድል ሆኖ አልታይሽ አለኝ :: ነገሩ የኢህአዴግ መንግስት ከአረጁ አይበጁነት ያመጣው ካልሆነ ሌላ አይደለም ::