የስርአቱን የገቢ ምንጭ በማንጠፍ እንዋጋው:: አስራትና በኩራት ስለትም ለገዳዮች መስጠት ይቁም
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
አስራትና በኩራት ስለትም ለገዳዮች መስጠት ይቁም ለቤ/ክ የሚሰጠው አስራትና በኩራት የስለት ከፍተኛ ገቢም ወደማን እንደሚገባ ያውቃሉ ??
ወደመንግስት ካዝና ገብቶ እኛኑ ለሚገድሉ አጋዚ-ፌደራል – ፖሊስ ደሞዝ አበልና እንክብካቤ እኛኑ ለመጨፍጨፍ ጥይት መግዣ ይውላል::
የተረፈው ስርአቱ ቆብ ቀሚስ አልብሶ በ17 ቱም የኦርቶዶክስ መምሪያ በደብር በሰበካ ጉባኤ ወዘተ ባሰማራቸው ነጣቂዎች ይዘረፋል ይበላል:: ከእንግዲህ ሌባ ስርአትን በገንዘብ በመደገፍ የራሳችንን መግደያ በገንዘብ አንደግፍም:: አስራትና በኩራት ስለትም መስጠት መጽሃፍ ቅዱሳዊ ቢሆንም ሃላፊነት ለጎደለው የቤ/ክ ካድሬ መስጠት ግን ግዴታ አይደለም:: በም ትኩ በገጠር ላሉ ቀሳውስትና ካህናት እንላክ:: በከተማ ላሉ ችግረኛና ረጂ ላጡ ምስኪኖች አረጋዊያን መጦሪያና ህጽናት ማሳደጊያ ድርጅቶች በስጦታ እናበርክት::