አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ወደ ኢትዮጵያ እንደማይመለስ አስታውቋል ኢትዮጵያውያን 43 ሺሕ ዶላር አሰባስበውለታል


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ወደ ኢትዮጵያ እንደማይመለስ አስታውቋል ኢትዮጵያውያን 43 ሺሕ ዶላር አሰባስበውለታል VOA Amharic

የ26 ዓመቱ ፈይሳ ሌሊሳ በትናንትናው በሪዮ ኦሎምፒክ የወንዶች ማራቶን የብር ሜዳልያ ያሸነፈበትን ሩጫ አጠናቆ ሲገባ በኦሮሞ ተቃውሞ ጊዜ የተጀመረውና በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ የተቃውሞ ምልክት የሆነውን እጅ ማጣመር ምልክት እያሳየ ገብቷል።

ይህን በማድረጉም ወደ ኢትዮጵያ ቢመለስ የግድያ ፣ የእስራት እና ፓስፖርት መቀማት ስጋት ስላለበት ወደ ሀገሩ እንደማይመልስ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ እንደሌሎቹ የኢትዮጵያ አትሌቶች ሜዳልያ ያመጣ ብሄራዊ ጀግና ነው፤ ሃሳቡን በነጻነት መግለጽ ይችላል፤ ወደ ሀገሩ ቢመለስ ምንም ዓይነት ጉዳት አይደርስበትም ብሏል።

አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ በበኩሉ የኢትዮጵያ መንግሥት ሁሌም ስለሚዋሽ በምን አምነዋለሁ? ብሏል።

በሌላ በኩል በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ፈይሳ ሌሊሳን የሕግ ድጋፍ እንዲያገኝ በሰዓታት ውስጥ ወደ 43 ሺሕ ዶላር ወይም ወደ 1 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር አሰባስበዋል።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

 በ2008 ዓ.ም ሪዮ ኦሎምፒክ በማራቶን ውድድር የብር መዳልያ ተሸላሚ ፈይሳ ሌሊሳ በሽልማት ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት