የአዲስ አበባው “ሰልፍ” – ግርማ ሰይፉ


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


በእኔ እምነት ዛሬ በአዲስ አበባ ተጠርቶ የነበረው ሰልፍ በስኬት በመከናወን ላይ ነው፡፡ ጠሪዎቹም የተጠራባቸውም እንዴት እንደሚገመግሙት ባላውቅም ማለቴ ነው፡፡

ቅዳሜ ቀን ሙሉ በዋና ዋና የከተማ ቦታዎች የውጭ ወራሪ የመጣ ይመሰል ከተማዋ በሠራዊት ተወራ ውላ ምሸቱን ሰዎች ከተለያየ አቅጣጫ ሲንቀሳቀሱ በፍተሻ ሰም ሲዋከቡ ነበር፡፡ ይህ ፍተሻ መቼም ፖሊሶቹ ሰራ ከምንፈታ ብለው ሳይሆን ጌቶቻቸው ባደረባቸው ጭንቀት ምክንያት አንድ ነገር እንዳይፈጠር በመስጋት እንደሆነ ግልፅ ነው፡፡

ቤቴ ስገባ መንገዱ ሁሉ ተወጥሮ ፖሊሶች በፍተሸ ላይ ናቸው፡፡ ለማነኛውም እውቅና ሳይጠየቅ የተሰጠው ሰልፍ በመንግሰት በኩል እውቅና እንዳገኘ ማሳያ ይመስለኛል፡፡ ለማነኛውም ማስፈቀድ የሚባል ህግ በሌለበት ካልፈቀድን ህገወጥ ነው አሉ እንጂ ህዝቡ ወጥቶ ምን እንደሚል መስማት ብቻ ሳይሆን ማድመጥ ይጠቅማቸው ነበር፡፡

ዛሬም እሁድ ሚያዚያ 30/97 በሚያስታውስ ሁኔታ ዶፍ እስኪወርድ ድረስ ከተማዋን የወረራት ሠራዊት ዞር አላለም ነበር፡፡ እነዚህ መሳሪያ የታጠቁ ሰዎች መቼም ወንድሞቻችን መሆናቸው ነው፡፡ የትላንት የቀኑ ቅዝቃዜ፣ የማታው ቆፈን የሚያሲዝ ብርድ እንዲሁም የቀኑ ብርድና ዝናብ እንደሚያስመርራቸው ጥርጥር የለወም፡፡

ጉዳይ ሀገር ሊወር ከመጣ ጠላት ጋር ቢሆን በሆታና በጭፈራ የሚታለፍ ነው፡፡ በጀግንነት ለመወጣት ከውስጥ ደም የሚሞቅበት ነው፡፡ የገዛ ወንድምና እህት ብሶቱን ለማሰማት እንዳይወጣ መጠበቅ ሲሆን ግን የሚቻል አይደለም፡፡ ደም አያሞቅም፣ ጀግና አስብሎ አያሸልምም፡፡

ሠራዊቱን ያሰጨነቀ፣ ማነኛውም የደህንነት ሰራተኛ ከወትሮ በተለየ በተጠንቀቅ፣ ካድሬዎች ከመደበኛ ስራቸው ውጭ ህዝብን እንቅስቃሴ እንዲከታተሉና ሪፖርት እንዲያደርጉ ያስገደደ፣ በተለይ በተለይ ደግሞ ገዢዎች በጭንቅ ውስጥ መሆናቸው ይፋ የሆነበት በመሆኑ ሰልፉ በስኬት ተከናውኖዋል ማለት ነው፡፡

በእርግጠኝነት የአዲስ አበባ አንድ አንድ ነዋሪዎች የሚሉትን በዜና እወጃ እንሰማለን …..

ጎበዝ ቤቴ ስገባ መንገዱ ሁሉ ተወጥሮ ፖሊሶች በፍተሸ ላይ ናቸው፡፡ ለማነኛውም እውቅና ሳይጠየቅ የተሰጠው ሰልፍ በመንግሰት በኩል እውቅና እንዳገኘ ማሳያ ይመስለኛል፡፡ ለማነኛውም ማስፈቀድ የሚባል ህግ በሌለበት ካልፈቀድን ህገወጥ ነው አሉ እንጂ ህዝቡ ወጥቶ ምን እንደሚል መስማት ብቻ ሳይሆን ማድመጥ ይጠቅማቸው ነበር፡፡