ሰልፍና ዓመፅ! (አብርሃ ደስታ)


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ ሰለፍ ተጠርቶ እንደነበር ሰማሁ። ሰልፍ የወጣው ግን ህዝብ ሳይሆን ፌደራል ፖሊስ ነበር አሉ። ህዝብ ሰልፍ ይወጣል ሲባል ሰልፉን ለማፈን ወታደር ወጣ። ሰልፍ ሰለማዊ (ሕጋዊ) ወይ ዓመፅ ሊሆን ይችላል። መጀመርያ በህጉ የተፈቀደው (ወይ የሚፈቀደው) ሰለማዊ ሰልፍን ነው። ህዝብ ጥያቄውን ወይ ቅሬታውን ወይ ተቃውሞውን በሰለማዊ መንገድ የመግለፅ መብት አለው። ሰለማዊ ሰልፍ ማድረግ መብት ነው። አንድ መንግስት ሰለማዊ ሰልፍን ከከለከለ ዓመፅን ፈቀደ ማለት ነው። ምክንያቱም ህጋዊ የሆነውን ነገር መከልከል ማለት ህጋዊ ያልሆነውን መፍቀድ ማለት ነው። ሰለማዊ ሰልፍን ለማፈን ከተጋ ሰለማዊ ያሆነውን መንገድ አበረታታ ማለት ነው።
ዛሬ በርካታ ፖሊሶች ሰለማዊ ሰልፈኞችን ለማሰርና ለመደብደብ ሲዘጋጁ ህዝብ መብቱን ተረግጦ ህጋዊው መንገድ ትቶ (ምክንያቱም አይተገበርም) ሌላኛው መንገድ (ዓመፅ) እንዲመርጥ እያስገደዱት ነው። ምክንያቱም ህዝብ ጥያቄ አለው። ጥያቄ ስላለው ነው ሰለማዊ ሰልፍ ለማድረግ የሚነሳው፤ ጥያቄ ባይኖረው ሰልፍ ለመውጣት አይነሳሳም ነበር። ህዝብ በሰለማዊ መንገድ (ሰለፍ) ጥያቄው እንዳያቀርብ በሐይል ማገድ፣ መከለከል ጥያቄው አይመልሰውም። ህዝቡ ሰልፍ ተከልክሎ ቢታፈንም ጥያቄው ይኖራል፣ አልተመለሰም። ስለዚህ ዓፈና ዓፈና እየወለደ የህዝቡ ብሶት ይገነፍልና ዓመፅ ወልዶ ጎርፍ ሆኖ ብዙ ህይወትና ንብረት እንዲወድም ምክንያት ይሆናል።

ስለዚህ የዓመፅ ዋነኛ ምንጭ ዓፈና ነው። ዓፋኙ ማነው? ኢህ አዴግ ነው። ሰልፈኞችን በማፈን ከሰለማዊ መንገድ ወደ ዓመፅ መንገድ እንዲሸጋገር እያደረገው ነው። ስለዚህ ኢህአዴግ ማፈኑን እስከቀጠለ ድረስ ዓመፅ መነሳቱ ስለማይቀር በዓመፁ ምክንያት ለሚፈጠር ኪሳራ ተጠያቂው ራሱ ኢህአዴግ ነው። ኢህአዴግ የዓመፅ መንስኤ ነው። የዓመፅ ምንጭ ጭቆና ነው። የጭቆና ምንጭ አምባገነን ስርዓት ነው። ጭቆና ባይኖር ዓመፅ አይኖርም ነበር። ሰለማዊ ሰልፍ ቢፈቀድ ዓመፅ አይኖርም ነበር። ሰለፍ ከተፈቀደ ሰው ለምን ያምፃል? ሰለማዊ ሰልፍ ካልተፈቀደለት ግን ዓመፅ ሌላው አማራጭ ያደርገዋል። ምክንያቱም ጭቅና ሲበዛ ይመራል፣ ከዓቅም በላይ ይሆናል። ከዓቅም በላይ ሲሆን ይፈነዳል፤ ሲፈነዳ ዓመፅን ይወልዳል። ስለዚህ ዓመፅን ለመከላከል ሰለማዊ ሰልፍን መፍቀድ ነው። ሰልፍን በጠመንጃ ሐይል ማገድ ዓመፅን መፍቀድ ነው።
It is s!!!

==========
በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ ሰለፍ ተጠርቶ እንደነበር ሰማሁ። ሰልፍ የወጣው ግን ህዝብ ሳይሆን ፌደራል ፖሊስ ነበር አሉ። ህዝብ ሰልፍ ይወጣል ሲባል ሰልፉን ለማፈን ወታደር ወጣ። ሰልፍ ሰለማዊ (ሕጋዊ) ወይ ዓመፅ ሊሆን ይችላል። መጀመርያ በህጉ የተፈቀደው (ወይ የሚፈቀደው) ሰለማዊ ሰልፍን ነው። ህዝብ ጥያቄውን ወይ ቅሬታውን ወይ ተቃውሞውን በሰለማዊ መንገድ የመግለፅ መብት አለው። ሰለማዊ ሰልፍ ማድረግ መብት ነው። አንድ መንግስት ሰለማዊ ሰልፍን ከከለከለ ዓመፅን ፈቀደ ማለት ነው። ምክንያቱም ህጋዊ የሆነውን ነገር መከልከል ማለት ህጋዊ ያልሆነውን መፍቀድ ማለት ነው። ሰለማዊ ሰልፍን ለማፈን ከተጋ ሰለማዊ ያሆነውን መንገድ አበረታታ ማለት ነው።
ዛሬ በርካታ ፖሊሶች ሰለማዊ ሰልፈኞችን ለማሰርና ለመደብደብ ሲዘጋጁ ህዝብ መብቱን ተረግጦ ህጋዊው መንገድ ትቶ (ምክንያቱም አይተገበርም) ሌላኛው መንገድ (ዓመፅ) እንዲመርጥ እያስገደዱት ነው። ምክንያቱም ህዝብ ጥያቄ አለው። ጥያቄ ስላለው ነው ሰለማዊ ሰልፍ ለማድረግ የሚነሳው፤ ጥያቄ ባይኖረው ሰልፍ ለመውጣት አይነሳሳም ነበር። ህዝብ በሰለማዊ መንገድ (ሰለፍ) ጥያቄው እንዳያቀርብ በሐይል ማገድ፣ መከለከል ጥያቄው አይመልሰውም። ህዝቡ ሰልፍ ተከልክሎ ቢታፈንም ጥያቄው ይኖራል፣ አልተመለሰም። ስለዚህ ዓፈና ዓፈና እየወለደ የህዝቡ ብሶት ይገነፍልና ዓመፅ ወልዶ ጎርፍ ሆኖ ብዙ ህይወትና ንብረት እንዲወድም ምክንያት ይሆናል።

ስለዚህ የዓመፅ ዋነኛ ምንጭ ዓፈና ነው። ዓፋኙ ማነው? ኢህ አዴግ ነው። ሰልፈኞችን በማፈን ከሰለማዊ መንገድ ወደ ዓመፅ መንገድ እንዲሸጋገር እያደረገው ነው። ስለዚህ ኢህአዴግ ማፈኑን እስከቀጠለ ድረስ ዓመፅ መነሳቱ ስለማይቀር በዓመፁ ምክንያት ለሚፈጠር ኪሳራ ተጠያቂው ራሱ ኢህአዴግ ነው። ኢህአዴግ የዓመፅ መንስኤ ነው። የዓመፅ ምንጭ ጭቆና ነው። የጭቆና ምንጭ አምባገነን ስርዓት ነው። ጭቆና ባይኖር ዓመፅ አይኖርም ነበር። ሰለማዊ ሰልፍ ቢፈቀድ ዓመፅ አይኖርም ነበር። ሰለፍ ከተፈቀደ ሰው ለምን ያምፃል? ሰለማዊ ሰልፍ ካልተፈቀደለት ግን ዓመፅ ሌላው አማራጭ ያደርገዋል። ምክንያቱም ጭቅና ሲበዛ ይመራል፣ ከዓቅም በላይ ይሆናል። ከዓቅም በላይ ሲሆን ይፈነዳል፤ ሲፈነዳ ዓመፅን ይወልዳል። ስለዚህ ዓመፅን ለመከላከል ሰለማዊ ሰልፍን መፍቀድ ነው። ሰልፍን በጠመንጃ ሐይል ማገድ ዓመፅን መፍቀድ ነው።
It is s!!!