“እንዳትረግጡት…. የኢትዮጵያን ዐፈር- መሬት! ”
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
‘ባካችሁ ……… ’ባካችሁ……….
እናንት በምድረ– ኢትዮጵያ ያላችሁ፤
“አትሂዱ …..በ‘ግራችሁ…”
ከቻላችሁ ….. “ብረሩ ክንፍ አው’ታችሁ።”
ግን…….. አደራ……….. ……….
አንዳትረገጡት ……. መሬቱን
እንዳታዩት……… አፈሩን፤
ብታርሱት…… አትዘሩበት
ብዘሩበት …….. አይበቅልበት፤……..
ደም ነውና – የትላንና– የዛሬ – የአሁን፣ ትኩስ…. የፈሰሰበት
አጥንት ነውና ያልደረቀ ፣ “አጸደ–ህይወት” የወደቀበት
እናንተም ከእንግዲህ ፣ ”ዐጽም – ‘ርስቴ” የማትሉት፤………..
ያውም ………………………………..
የባቶቻችሁ፣…….. የናቶቻችሁ
ያውም………………………………
የወንድሞቻችሁ፣…….. የህቶቻችሁ
ያውም……………………………………
የእቦቀቅላወቹ፣…… የታዳጊወቹ፣……..የልጆቻችሁ፤
ዓይናችሁ እያየ፣……. እየሰማ ጆሮ‘ችሁ
የተመቱ! … የቆሰሉ!….. የተወጉ! …. የተፈነከቱ!…..
የተቀጠቀጡ!…. የተዘለዘሉ!……! ……የተረሸኑ!
….. በገዛ ወገኖቻችሁ………..
ያውም …………”ወገን እኮ ነን “ እያላችሁ።
በደመዋ ልባችሁ……………………………….
“ኤሉሄ …..ላማ ሰበቅተኒ!”……. ብላችሁ
ወሰን – ድንበር ለሌለው ሰቆቃችሁ
ብትነግሩትም “ለሰማይ አባታችሁ”፤
ግን….. ለምንም – ለማንም አይመችም
ሀዘናችሁ መልክ የለውም……….
ያልተነገረ እንጅ፣ ያልተፈጸመባችሁ ግፍ የለም።
ብትጎጉጡ፣ ደም አልቅሳችሁ፣….. እየየ …ብላችሁ –
ቢያዳርስም ዓለም ….. ሲቃ – ዋይታችሁ …
መቼም– መቼም ቢሆን፣ ምንጩ አይደርቅም የ‘ምባችሁ::…..
እናማ………………………………………..
ሰላም፣ ፍትህ፣ እኩልነት – ሳታሰፍኑ – በመሀከላችሁ
አንድነትን ሳታነግሱ – በምድራችሁ
ይቅር ሳትባባሉ፣ ‘ርስ – በርሳችሁ
ሳይመለስ ክብራችሁ፣ ጠፈር – ድንበራችሁ
የድል ችቦው – ከፍ ሳይል ፣ ክብር ሰንደቅ ዓላማችሁ፤……
የወገናችሁን ደምና– አጥንት እንዳትረግጡት
“ይወጋችሁልና እሾኽ ሆኖ፣ የኢትዮጵያ ዐፈር – መሬት!”።
———//———
ፊልጶስ/ ነሀሴ 2008
E-mail: [email protected]