በአልሸባብ በጸረ ሰላም ሃይሎች እና በሻእቢያ ስም ሽፋን ፍንዳታዎችና ዘረፋዎች ሊፈጸሙ ነው


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


በአልሸባብ በጸረ ሰላም ሃይሎች እና በሻእቢያ ስም ሽፋን ፍንዳታዎችና ዘረፋዎች ሊፈጸሙ ነው ።
‪#‎StateTerrorism‬ in ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎TPLF‬ ‪#‎Alshebab‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ ‪#‎Eritrea‬

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) የኢጋድ መረጃ ነው በሚል ሽፋን ሕዝብንና ምእራባውያንን ለማታለል የወቅቱ የኢጋድ ሊቀመንበር የኢጋድ ማህተምና ኣስፈላጊ የኢጋድ መብቶች በእጁ የሚገኘው ሕወሓት እየበሰበሰ በመፍረክረክ ላይ የሚገኘው የሕወሓት ስርአት በመላው ሃገሪቱ ከፍተኛ ፍንዳታዎች እና ዘረፋዎችን ለመፈጸም ማቀዱን ከደህንነት አካላት የተገኙ ምንጮች ጠቁመዋል፥፥ይህ ፍንዳታ እና ዘረፋ አልሸባብ እያለ ራሱ የሚጠራውን ድርጅት ላይ ለማላከክ እና አልሸባብን ለመወንጀል ዝግጅቱ የተጠናቀቀ ሲሆን ከፍተኛ ፍንዳታዎች ይካሄዳሉ የተባለው በስፋት በመሃል ሃገር በገጠር መንገዶች ትራንስፖርቶች እንዲሁም በክልል ከተሞች መሆኑ ተጠቁሟል፤ያለውን የተኩስ ግለትና የፖለቲካ ጡዘት አየሮች እየተከተለ በወያኔ ቅጥረኞች እንደሚፈጸምም ታውቋል።

Image may contain: 1 person , text

እንዲሁም በከፍተኛ የገንዘብ ተቋማት የመንግስት መስሪያ ቤቶች የግል ድርጅቶች እና የባለሃብቶችን ገንዘብ ለመዝረፍ መታቀዱን እነዚሁ የደህነት አካላት የተናገሩ ሲሆን ለዚሁ ጉዳይ የተደራጀ አካል ከሕወሓቶች እየተዘጋጀ መሆኑን ምንጮቹ አክለው ገልጸዋል፤ የህዝብ ንቅናቄ ጥርስ ውስጥ የገባው ወያኔ በምእራባውያን ሳይቀር ስልጣኑን እንዲልቅ ቢፈለግም አንቆ የያዝው ሲሆን ስልጣን ብንለቅ መጪው መንግስት ከገባንበት ቆፍሮ ያወጣናል የሚል ፍራቻ እንዲሁም የህዝብ ንቅናቄ ከፍተኛ ውጥረት ፈጥሮበት ወያኔ አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው ሲሆን በህዝብ ሃይል እንደሚወገድ ኢትዮጵያውያ ብቻ ሳይሆኑ የውጪ ሃይሎችን ያመኑበት ጉዳይ መሆኑን ይታወቃል።

ከአልሸባብ ጋር ባለው ጉልህ ቁርኝት አገሪቷን የማመስ እቅድ እንዳለው በሚሰሙበት ወቅት ላይ የድንበር አከባቢዎች የሚሊሻዎችን ግጭት ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ ጦርነት ከኤርትራ ጋር በድንበር አከባቢዎች ማንዣበቡን በገሃድ እየታየ ነው፤ ሰራዊቱን ጨምሮ በደህንነቱ እና በተለያዩ የመዋቅር ተቋማት ውስጥ ያሉ ኢትዮጵያውያን በዘረኛው የወያኔ አገዛዝ እንደተንገሸገሹ እና የሚፈልጉት አስተማማኝ የሆነ ወያኔን ሊጥል የሚችል ሃይል ስለሆነ ካለምንም ማመንታት የህዝብን ንቅናቄ የሚያመጣውን የውድቀት ውጤት እንደሚቀበሉት ከድርጅቱ ውስጣዊ ውጥረት የተረጋገጠ ሃቅ ነው። ‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬ More Info – http://www.mereja.com/amharic/509458