የ እስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚንስተር ዜጎቹ ወደ ኢትዮጵያ ከሚያደርጉት ጉዞ እንዲቆጠቡ አስጠነቀቀ ።
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
የ እስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚንስተር ዜጎቹ ወደ ኢትዮጵያ በተለይም ወደ ጎንደር እንዲሁም ኦሮሚያ ብሎም ወደ አዲስ አበባ ከሚያደርጉት ጉዞ እንዲቆጠቡ አስጠነቀቀ ። Minilik Salsawi
ሰሞኑን በጎንደር በነበረው ግጭት ሰዎች በመሞታቸውና እንዲሁም በቀጣይ ተከታታይ ቀናት ሰላማዊ ሰልፎች ይካሄዳሉ የሚል መረጃዎች እየወጡ ስለሆነ ማንኛውም የ እስራኤል ዜጋ ወደ ቦታው በተለይም ሰላማዊ ሰልፎች ወደ ሚካሂድበት አካባቢ እንዳይቀርብ የውጭ ጉዳይ ሚንስተር አስጠንቅቋል
በተጨማሪም በኢትዮጵያና ኤርትራ እንዲሁም ኢትዮጵያና ሱዳን ፣ ኬኒያ – ኢትዮጵያ ፣ደቡብ ሱዳን በሚያዋስኑት ደንበሮች አካባቢ 10 ኪሎ ሜትር ወደ ቦታው ማንኛውም የ እስራኤል ዜጋ እንዳይቀረብ መክረዋል። ከላይ በተጠቀሱት ቦታዎችና ስፍራዎች አካባቢ ማንኛውም እስራኤላዊ ዜጋ ቢገኝ በራሱ ሃላፊነት እንደሆነ የ እስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚንስተር አስጠንቅቋል።