“ጀግናው ይፈታ፣ ጀግናው ይፈታ” በማለት ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ ጉዳዩውን በአይነ ቆራኛ ሲከታተል ቆይቶአል
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
ጀግናው ይፈታ ጀግናው ይፈታ በማለት ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ ጉዳዩውን በአይነ ቆራኛ ሲከታተል ቆይቶአል። #MinilikSalsawi
ኮሌነር ደመቀ ፍርድቤት አልቀረቡም ወደ ሰኞ ተራዝሟል የከተማው ሰው በነቂስ ወጥታል በአሁን ስዓት ወደ መስቀል አደባባይ ቅስቀሳ ለማድረግ ከወህን ቤቱ እየተመለሰ ነው ። እውነት እላቹሀለው ወያኔ ፈርቷል!!!
የሰሜን ጎንደር ዞን ከፍ/ፍ/ ቤት ተወካይ ፕሬዝዳንት አቶ ባህሩ አዲስ በዛሬው ዕለት የኮ/ል ደመቀ ዘውዱ የጊዜ ቀጠሮ ቢኖርም በመንግስት ርካሽ ተወዳጅነትን ለማትረፍ ብሎም ፕሬዝዳንት ሆኖ ለመሾም ሲል በዳኞች ላይ ጣልቃ በመግባት ኮሎኔሉ ችሎት ሳይቀርብ ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ ለፖሊስ ፍቀዱ በሚል ከዳኞች ጋር ዝግ ስብሰባ ይዟል:: ቀጠሮው ጥዋት ላይ የነበረ ቢሆንም ከሰዓት በኋላ በሚል የተራዘመው በዚሁ የተነሳ ውዝግብ በመፈጠሩና መግባባት ባለመቻሉ ነው!!
ዳኞችም ኮሎኔሉ ችሎት የመቅረብ ህገመንግስታዊ መብት እያለው ሳይቀርብ ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ መፍቀድ አግባብ አለመሆኑን በመግለፅ እስካሁኗ ስዓት ድረስ በአቋማቸው ፀንተው ቀጥለዋል!!
የከፍተኛ ፍ/ቤቱ ተወካይ ፕሬዝዳንት አቶ ባህሩ አዲስ ግን የኮለኔሉን መብት በማፈን ለመሾም ለመንግስት የእጅ መንሻ አድርጎ ማቅረቡንና ዳኞችንም ጭምር ሊያስበላ የተዘጋጀ አድር ባይነት የተጠናወተው ሰው ስለሆነ ጀግናው የጎንደር ህዝብ ጥብቅ ክትትል ሊያደርግበት ይገባል!!
