ኢሕአፓ ለጎንደር ሕዝብ ትግል ሙሉ ድጋፉን ያረጋግጣል !!!
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
ኢሕአፓ ለጎንደር ሕዝብ ትግል ሙሉ ድጋፉን ያረጋግጣል !!!
#Ethiopia #Amharaprotests #EPRP #Gonderprotests #MinilikSalsawi
በኢሕአፓ የትግል ታሪክ ውስጥ ጎንደርና የጎንደር ሕዝባ ያላቸው ቦታ ከፍተኛ ነው ። የጎንደር ሕዝብ ኢሕአፓንም ሌሎች ሀገር ወዳድ ድርጅቶችንም ደግፎ ከፍተኛ መስዋዕትነትን ከፍሏል ። አራጁ መላኩ ተፈራና አረመኔው ደርግ ፤እንዲሁም ዘረኛውና ጸረ አማራው ወያኔ ይህን ታጋይና ሀገር ወዳድ ሕዝብ በተለየ ደረጃ አጥቅተውታል ። የጎንደር የሰማዕት ታሪክ የኢሕአፓ ታሪክ ማዕክል ሆኖም ቆይቷል ።
ኢሕአፓ በጎንደር እየተካሄደ ያለውን ጸረ ወያኔ ትግል ሙሉ በሙሉ ይደግፋል ። ወያኔም ማጥቃቱ፤ንብረታቸውን በእሳት ማጋየቱ፤ መሬትና ማንነትን ለማስክበር ቆርጦ መነሳቱን ያደንቃል ። የሕዝብ ቁጣ ሊያበርዱና ሊያሰናክሉ፤ ሰላም በሚል ቀረርቶ ትግልን ሊያኮላሹ፤ በፖለቲካና ኢትዮጵያዊነት ዙሪያ ማበር መደራጀት ሲገባ የጎጥ ሰልፍና ልማት ተብዬውን ሊሰብኩ የተነሱትን ሁሉ ኢሕአፓ ያወግዛል ። ወቅቱ የመራራና የቆራጥ ትግል ወቅት ነው ። ወያኔ ሕዝብን በጅምላ በመፍጀት ትግሉ ለማፈን መጣሩ የሚጠበቅ ነው ። በግድ ወደ ትግራይ የተጠቃለለው መሬትና ማንነቱ የተካደውም ሕዝብ ቆርጦ መነሳቱ የሚመሰገን ነው ። የአፍራሽና የቅጥረኞች አዞ እንባ ረግጦ ትግልን መቀጠል አስፈላጊ መሆኑን ትግልን ለሚያውቀው የጎንደር ሕዝብ ሊያስተምር የሚቃጣ ሊኖርም አይችልም ።
ከጎንደር ሕዝብ ጎን በተጨባጭ መቆም ጊዜው አሁን ነው ። ሀገርን ማስመለስና ድንበርን ማስከበር፤ ማንነትን ማስረገጥ ለነገ የሚባል ትግል አይደለም ። በመሆኑም ኢሕአፓ በአካባቢው ያሉትን አባላትና ደጋፊዎች የትግሉ አካል ሆነው እንዲሰለፉ ጠርቷል ። በሰበብ አስባቡም ከወያኔ ጎን ቆመው የነበሩትም በጊዘ ከሕዝብ ጎራ እንዲቀላቀሉም ጥሪ ያደርግላቸዋል ። ይህ ጸረ ወያኔ ትግል መጠቃት የለበትምና ሀገር ወዳድ ሀይሎች ሁሉ– በያሉበት–ሊታደጉት፤ሊረዱት፡ሊያጠናክሩት መነሳት አለባቸውም ይላል ።
ከዚህ ተያይዞ መነሳት ያለበት ዋናው ጉዳይ ግን የጎንደር ሕዝብ ላይ የሚደርሰውን ጥቃት በተመለከተ ባእዳን ዝምታን መምረጣቸውን ነው ። ጸረ አማራው የወያኔ ፖለቲካ ከእነዚህ ክፍሎች ከድሮ ጀምሮ ሲደገፍ የቆየ ነውና የሕዝቡ ትግል ማስተጋባትም ሆነ ለድል ማብቃት የኢትዮጵያውያን ግዳጅ ሆኖ ይገኛል ። የጎንደር ሕዝብ አመጽ ወያኔ ሊል እንደሞከረው የባዕድ ታጣቂ ሀይሎች እርምጃ ሳይሆን፤የማንም ድርጅት ድርጊት ሳይሆን የሰፊው ሕዝብ የእምቢታ ውጤትና አመጽ መሆኑ መታወቅም ያለበት ነው ።
ኢሕአፓ ከጎንደር ሕዝብ ጎን ተሰልፏል !!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!
EPRP
P.O.BOX 73337 Washington DC, 20056 USA
Tel. 202 291 4217 Fax: 202 291 7645
Email [email protected]
Website www.eprp.com
EPRP
BP 30022
92276 Bois Colombes cedex
France
