ገመና ሸፋኞች ሆይ፣ የተዘራ ይታጨዳል!!! የትግራይ ተወላጆችን ሽፋን አድርጎ ሕወሓትን አትንኩብኝ ነጠላ ዜማ ይቁም !!!


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


ገመና ሸፋኞች ሆይ:-የተዘራ ይታጨዳል!!! የትግራይ ተወላጆችን ሽፋን አድርጎ ሕወሓትን አትንኩብኝ ነጠላ ዜማ ይቁም !!! ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Tigray‬ ‪#‎OromoProtests‬ ‪#‎Amharaprotests‬ ‪#‎TPLF‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬

Minilik Salsawi – mereja.com – በግልጽ ለሚገባው ብቻ ማስረዳት ይቻላል::ሕዝቡ እኮ ሁሉን ለይቶ ያውቃል::በላቡ ያፈራውን አብሮ የኖረውን እና በብዝበዛ የከበረውን መጤ ትግሬ በደንብ ያውቃል::አንዳንድ የአረና ትግራይ ፓርቲ ወዳጆቻችንና ከአለና የተለጠፉ አዛኝ ቂቤ አንጓች ጸሃፍያን የትግራይ ሕዝብን እና ሕወሓትን እንዲለዩ እየነገሩን ነው ማን እንደቀላቀለባቸው አላውቅም እንጂ ካሁን በፊት በተደጋጋሚ እንደምንናገረው የትግራይ ሕዝብ እና ሕወሓት ልዩነት አላቸው ከዚህ ጋር በተቆላለፈ ደግሞ የትግራይ ሕዝብን ስሙን መደበቂያ አድርገው ቀሪውን የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያጥቁ የሕወሓት ካድሬዎችና የትግራይ አይሁድን ለመመስረት ( https://www.facebook.com/permalink.php?id=291169534245718&story_fbid=911626555533343 ) ደፋ ቀና የሚሉ የሕወሓት የበላይ አካላት እና ተላላኪዎቻቸው ሲልም ሕወሓት እንዲወድቅ የማይፈልጉ በተቃዋሚ ካባ የሚደሰኩሩ የጊዜ ጀግኖች በተጨማሪም ከየተቃዋሚ ፓርቲ እንደ አረና-መድረክ ተመልምለው በጥሩ ኑሮ ውስጥ የሚርመጠመጡና ቻይና አውሮፓ እና ሰሜን አሜሪካ ለትምሕርት የተላኩና ተምረው የመጡ የትግራይ ወጣቶች የትግራይ ተወላጆችን ሽፋን አድርገው በጎንደሩ ሕዝባዊ ንቅናቄ ተገን ሕውሓትን አትንኩብኝ የሚል ነጠላ ዜማቸውን እየተነፈሱን ይገኛሉ::

በኦሮሞ ሕዝብ ይሁን አሁን ጎንደር ላይ በተነሳው ህዝባዊ ንቅናቄ ከፍተኛ ጉዳይ የደረሰው የሕወሓት አባላት በያዙት ንብረት እላ የሕወሓት የንግድ ድርጅቶች በሚመሩት ንብረት ላይ መሆኑ በመጀመሪያ የማወቅ ግዴታ አለብን::ሕወሓት የጎሳ ፖለቲካ ፍልስፍናውን በመላው ኢትዮጵያ ሲረጭ የዘራው የማያጭድ መስሎት አስቦ ቢሆንም ካሁኑ በባሰ ሁነታ የዘራውን እንደሚያጭድ ደጋግሞ ሊያስብበት ይገባል;ከግል ካምፓኒዎች ጀምሮ እስከ መንግስት መስሪያ ቤት በሕወሓት አባላት በወረራ የተያዘው የሕዝብ ስልጣን ንብረት እና መላው አገልግሎት ሌሎች ኢትዮጵያውያንን የመኖርና የመስራት ሕልውና አሳጥቷል::በማንኛውም መስሪያ ቤቶች ለጉዳይ ሲኬድ የሕወሓት አባላት የሕዝብን ስልጣን በቁጥጥር ስር ከማዋላቸውም በላይ የፈደራሉ ቋንቋ ትግሪኛ አስመስለውታል ጎን ለጎንም ዘረፋውን አጧጡፈውታል::በዚህ አጋጣሚ ስለ እዚህ የዘረኝነት መንፈስ የሚሰራ እኩያ ስራ የሚያሳስባቸውና ተጠቃሚ ያልሆኑ የትግራይ ተወላጆችን እንዳሉ ልንገነዘብ ይገባል::የሕወሓት አባላት ተጠቀሙ ዘረፉ ገደሉ ሲባል በስመ ትግሬ ሁሉም የትግራይ ተወላጅ ወንጀለኛ ነው ማለት አይደለም::ሆኖም ሕወሓት በሚነዛው ፕሮፓጋንዳ ራሱ በሕወሓት ሴራ ከኑግ የተገኘ ሰሊጥ አብሮ ተወቅጦ ሊሆን ይችላል::

ሕወሓት ባለፉት 25 አመታት ሲዘርፍ ሲገል ዜጎችን ሲያፈናቅል ሲያሰድድ ብዙሃኑ ድምጹን ሲያሰማ በሃገር ቤት እና በውጪ ሲጮህ አንድም ትንፍሽ ያላሉ ስለ ሌላው ሰብኣዊ መብት የማይታያቸው ዛረእ ላይ በየክልሉ ሕዝቡ ብሶቱ ሲገንጽ በገዛ እትብቱ መቃብር ላይ የፖለቲካ ጠበንጃ ያነገቱ ሕወሓቶች ሲዘርፉ የበይ ተመልካች አልሆንም በማለት ሲነቃነቅ እና ስርኣቱን ሲቃውም የስርኣቱ አሸርጋጆች የሆኑና በስርኣቱ የተጠቀሙ የትግራይ ተወላጅ የሕወሓት አባላት ንብረትን ሲያወድም የሚያሞጠሙጡ ሁሉ ዘረኝነት እንዴት እንደሆነ እያሳዩን ከመሆኑም በላይ የትግራይ ተወላጆች ከላይ እስከታች ዘረፋውን ሲያጧጡፉ ሲገሉ ሲያስሩ እና ሁሉን በሞኖፖል ሶይዙ ስልጣኑን ይዘው ሆዳሞችን ሲገዙ ግን ዘረኝነት አይታያቸውም::እነሱ ሲያደርጉት ዘረኝነት የለም ሌላው ግን የበይ ተመልካች አልሆንም ብሎ ሆ ሲል ዘረኝነት የሚባልበት ምክንያት በፍጹም አይገባንም::

በትግራይ የገባውን ችጋር የፈጠረው ሕወሓት መሆኑ አይካድም::ሕወሓት ከመጀመሪያው አነሳሱ የጸረ አማራ መርሃ ግብር ነድፎ እንደሚንቀሳቀስ ነግሮናል::ጎን ለጎን ታላቋን የትግራይ ሪፑብሊክ ለመመስረት እንደሚሰራም እያሳየን ነው::ለትግራይ ሕዝብ ከፍተኛ ፋብሪካዎች ሲገነቡ ለኦሮሞ ሕዝብ ግን የዘረኝነት እና የጥላቻ ሃእልት ሲቆም የአማእ ሕዝብ ደግሞ በተለያዩ መርዘኛ ከሚካሎችና መድሃኒቶች ይፈጃል::ይህ እንግዲህ የሕወሓት ስራ ነው ሕወሓት የዘራውን ማጨድ የሚጀምርበት ቀን ሩቅ አይደለም::ገና አልተነካም::ሕወሓትን ተገን አድርገው በየክልሉ ባለሃብት የሆኑ ሁሉ የገፈቱ ቀማሽ ናቸው::ይህ ማለት የትግራይ ተወላጆች ይመታሉ ማለት አይደለም::ሕዝቡ እኮ ሁሉን ለይቶ ያውቃል::በላቡ ያፈራውን አብሮ የኖረውን እና በብዝበዛ የከበረውን መጤ በደንብ ያውቃል::ይህ ለሕዝቡ ነጋሪ አያስፈልገውም::ሁላችንም ነጋሪ አያስፈልገንም::በትግራይ ሕዝብ ስም መነገድ እንደማይቻል እነግራቹሃለሁ ከተፈለገ ደግሞ ወሓትን እና የትግራይ ሕዝብን ለይታቹ የምታውቁበት ተጨማሪ ዝርዝር ማስቀመጥ ይቻላል ሕዝቡን አፍኖ የትግራይ ሕዝብና ሕወሓት አንድ ናቸው ማለት ተቀባይነት የለውም::ሕወሓት ከሞተ አንተም ትሞታለህ እየተባለ ለትግራይ ሕዝብ የሚነገረው ፕሮፓጋንዳ ፉርሽ ነው::በየክልሉ የጥቃት ሰለባ የሆኑት የሕወሓት ሰዎች ንብረቶች መሆናቸው ሙሉ በሙሉ የተረጋገጠ ነው::እኔ ‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬ አንድ ነገር እላለሁ :- ገመና ሸፋኞች ሆይ:-የተዘራ ይታጨዳል!!! የትግራይ ተወላጆችን ሽፋን አድርጎ ሕወሓትን አትንኩብኝ ነጠላ ዜማ ይቁም !!!

Minilik Salsawi's photo.