አሜሪካ ለድርቁ ተጎጂዎች የ128 ሚ. ዶላር ተጨማሪ እርዳታ ልትሰጥ ነው
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
የአሜሪካ የተራድኦ ድርጅት ዩኤስኤአይዲ፣ በኢትዮጵያ በተከሰተው ድርቅ ተጎጂ ለሆኑ ዜጎች 128 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ ተጨማሪ የሰብአዊ እርዳታ ለመስጠት መወሰኑን ከትናንት በስቲያ አስታወቀ፡፡
በዩኤስኤአይዲ የዲሞክራሲ፣ የግጭትና የሰብዓዊ ጉዳዮች ቢሮ ረዳት አስተዳዳሪ ቶማስ ኤህ ስታል፣ ተጨማሪ የሰብዓዊ ድጋፍ እርዳታው ምግብ፣ ንጹህ የመጠጥ ውሃ፣ የስነምግብ አገልግሎቶችና ተንቀሳቃሽ የጤና ቡድኖችን የሚያጠቃልል መሆኑንና ለአርሶ አደሮችም የተለያዩ የእህል ዘሮች እንደሚከፋፈሉ ተናግረዋል፡፡
ተጨማሪ እርዳታው አሜሪካ ድርቁ አስከፊ ሰብዓዊ ቀውስ እንዳያስከትል ለመከላከል ስታደርገው የቆየቺውን ጥረት አጠናክራ ለመቀጠል ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል ያሉት ስታል፣ አሜሪካ ከጥቅምት ወር 2014 አንስቶ፣ ለኢትዮጵያ 705 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ የሰብዓዊ ድጋፍ ማድረጓንም አስታውሰዋል፡፡