በሙኒክ ጀርመን ፀረ-ወያኔ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተደረገ::
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
በሙኒክ ጀርመን ፀረ-ወያኔ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተደረገ::
በዛሬው እለት በጀርመን ሰአት ከጠዋቱ ስምንት ሰአት ጀምሮ የኦሮሞ ኮሚኒቲ በሙኒክ እና ኢትዮጵያውያን አክቲቭስቶች ያዘጋጁት ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በጀርመን ሙኒክ መካሄዱን በቦታው የነበሩ የኢትዮጵያ ወጣቶች ድምጽ ምንጮች ገልጸዋል::
የሕወሓት ቁንጮ ባለስልጣን የሆነው ዶ/ር ቴወድሮስ አድሀኖም የወጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና በኢትዮጵያ ከግብረአበሮቹ ጋር የሚፈጽመውን ወንጀል እና ግፍ ለመቃወም የተጠራው ይህ ሰልፍ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረገውን ኢሰባዊ ድርጊት በማውገድ ድምጹን ሲያሰማ አርፍዷል::በርካታ ወገኖቻችን በሀገር ውስጥም በውጭም እንደ አመት በአል በግ ሲታረዱ ትንፍሽ የማይለው ዶ/ር ቴወድሮስ በየሀገሩ እየዞረ ስደተኞች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ የሚፈራረመው ቀልፍ የህወሓት ሰው በመሆኑ
ይህ ጸረ ኢትዮጵያ ሰው ለማውገዝ ኢትዮጵያውያን ከያሉበት ተሰብስበው ተቃውሟቸውን አሰምተዋል::