የእንግሊዛዊው ባለቅኔ ዊሊያም ሼክስፒር የራስ ቅል ከመቃብሩ መዘረፉ ተረጋገጠ
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
ከ400 አመታት በፊት ከዚህ አለም በሞት የተለየው እንግሊዛዊው ባለቅኔ ዊሊያም ሼክስፒር የራስ ቅል ከመቃብሩ ውስጥ ባልታወቁ ዘራፊዎች መሰረቁ በአርኪዎሎጂስቶች ጥናት መረጋገጡን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘገበ፡፡እንግሊዛውያን ተመራማሪዎች በስታንፎርድ የቅዱስ ስላሴ ቤተክርስቲያን ውስጥ በሚገኘው የዊሊያም ሼክስፒር መቃብር ላይ ባደረጉት የራዳር ፍተሻ፣ የባለቅኔው የራስ ቅል መቃብሩ ውስጥ እንደሌለ ማረጋገጣቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ የመቃብሩ የላይኛው ክፍልም ከረጅም አመታት በፊት ተከፍቶ እንደነበር የሚያሳይ ምልክት መገኘቱን ገልጧል፡፡
በዚሁ ምልክት ላይ በተደረገ ምርመራ፣ የራስ ቅሉ የተዘረፈው በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሳይሆን እንደማይቀር መገመቱ የተነገረ ሲሆን፣ የራስ ቅሉ መጥፋት የታወቀው ባለቅኔው ከዚህ አለም በሞት የተለየበትን 400ኛ አመት በማስመልከት ዶክመንተሪ ፊልም በሚሰራበት ወቅት መሆኑንም አስረድቷል፡፡ሼክስፒር ከሚወዳት ባለቤቱ አና ሃትዌይ ጎን መቀበሩን ያስታወሰው ዘገባው፣ የመቃብር ስፍራው ለረጅም አመታት በበርካታ የባለቅኔው አድናቂዎች ሲጎበኝ የኖረ ትልቅ ስፍራ እንደነበርም አክሎ ገልጧል፡፡