ውሃ በፈረቃ ፥ የሙታንን መነሳት ተስፋ እናደርጋለን ( ሄኖክ የሺጥላ )
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
ውሃ በፈረቃ ፥ የሙታንን መነሳት ተስፋ እናደርጋለን ( ሄኖክ የሺጥላ )
ኣንድ ወዳጄ አዲሱን የአዲስ ኣበባ “ውሃ በፈረቃ” ዜና እንደሰማ ፥ « ድሮ በምን ነበር ?» ብሎ የጠየቃት ጥያቂ ፈገግ ኣድርጋኛለች።
የኣዲስ ኣበባ የመሬት ትሎች ዛሬ ዛሬ ከኣፈሩ ይልቅ ለመኖሪያነት ቧንቧውን ይመርጣሉ። ለምን ቢሉ ኢትዮጵያ ውስጥ ውሃ ከሚመጣበት ቀን ይልቅ « መሬቱ ለ ኢንቨስትመንት ይፈለጋል እና ተነሱ» የሚለው የመንግስት ማስታወቂያ የሚሰማበት ይልቃልና።
ኣንደውም ኣንድ ዘመዴ « ጉዳዩ የውሃ ጉዳይ ሆኖብኝ እንጂ ይሄንንም ቧንቧ እንደ ኢቲቪ ጥርቅም ኣድርጌ ዘግቼው ባረፍኩ ነበር !» ያለችኝን ባነሳስ!
ለነገሩ ኣባይ ተገድቦ እንዳለቀ ፈረቃው ይቀራል ልል ብዬ ፥ ለካስ ኣባይ ለመጠጥ የሚሆን ውሃ የለውም ለግድብ እንጂ! ብዬ ያባይን ነገር ለግብፆች ትቼ ወደ ኣዋሽ ገሰገስኩ ። ኣዋሽ ስደርስ ኣዋሽ ከነ ኣባ ሳሙኤል እና ገፈርሳ ጋ ኣምስት ለኣንድ ኣልጠፈነግም ብሎ ፥ ህገ መንግስቱም ኣይመለከተኝም ብሎ እንደ ዋቢ ሸበሌ ኣሸዋ ውስጥ መኖር እንደጀመረ ሰማሁ ።
በነገራችን ላይ በወንዞች የተከበበችው ሸገር ውሃ ሲጠማት ትግራይ እንዴት ኣድራ ይሆን ?
ማን ነበር
« ኣይጫንም እንጂ ውሃ በመኪና
መቀሌ ነበሩ ኣባይና ጣና » ያለው ።
እነሱ ምናቸው ሞኝ ነው በመኪና የሚጭኑልህ ሃይላንድ እያለ!
ኣዲስ ኣበቤዎች የክርስቶስን ፥ የውሃን እና የመብራትን መምጫ እስከ ዛሬ ኣያውቁትም ነበር ፥ ዋን ኢዝ ዳወን ናው ። መብራትም በፈረቃ ሆነ የሚለውን ዜና ስንሰማ ምናልባት ያኔ « የሙታንንም መነሳት ተስፋ እናደርጋለን !» ብለን ካንጀታችን እንፀልያለን ። ሲሆን ስላየን!
