ጠቅላይ ሚኒሰትራችነ ነጋዴዎች እስር ቤት እንዳላቸው ነገሩን::እስር ቤት ያደራጁ ነጋዴዎች ካሉ በይፋ ለህዝብ ይፋ መደረግ ይኖርበታል፡፡


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


ባለፈው ማክሰኞ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምሁራን ጋር ውይይት ደርጋሉ የሚለውን መረጃ ሰምቼ፣ ቅርባቸው ነው ላልኩት ሹም በስብሰባው እንድገኝ ጥያቄ አቅርቤ ነበር፡፡ ዋናው ምክንያቴ ባለፈው ምክር ቤት ተገኝተው ባቀረቡት ሪፖርት ላይ አንድም የምክር ቤት አባል የሪፖርታቸውን ይዘት መሰረት አድርጎ በዚህ ገፅ በዚህ መስመር እንዲህ የሚለው ልክ አይደለም ማለቱ ቢቀር ይብራራ የሚል ሰው ባለማግኘታቸው በዚሁ አጋጣሚ እድል ቢያገኙ በሚል ነበር፡፡ ለማነኛውም የተገኙት ተሳተፊዎችም ቢሆኑ የዋዛ የማይባል ጥያቄ ማንሳታቸውን እኛ አድማጮ ደግሞ በተሰጠው ማብራሪያ ሳይሆን በጥያቄዎቹ መስመር ላይ መሆናችንን ማሳታወስ ግድ ነው፡፡ ምን ማለት ነው፡፡ ይህች ሀገር ነፃነት ያለው ህዝብ መኖሪያ አይደለችም፡፡ ጋዜጣኛም፣ ነጋዴም፣ ፖለቲከኛም፣ ተማሪም፣ ወዘተ በነፃነት የሚኖርበት ሀገር አይደለም፡፡ ጠቅላይ ሚኒሰትሩ ደረታችሁን ነፍታችሁ የምትሄዱት በሚል ከናይሮቢ ጋር ያደረጉት ንፅፅር በምንም መመዘኛ ትክክል አይደለም፡፡ ኬኒያዊ የኬኒያ መንግሰት ስጋቱ አይደለም፡፡ እኛ ግን መንግሰታችን ስጋታችን ነው፡፡ በእኛ ሀገር ሀፈና የሚፈፀመው ሊጠብቅህ በሚገባ መንግሰት ነው፡፡ ኢትዮጵያ ደግሞ እስከ ዛሬ ከሸብርተኛ ቡድን ነፃ የሆነችውን ጠቅላይ ሚኒሰትሩ ስምም ፆታም አልገልፅም ብለው ነገር ግን እስከ አያት ስሟ የነገሩን ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ጉቤቦ በማሰራቸው አይደለም፡፡ ኢትዮጵያዊ በዚህ ደረጃ ለሸብር የደረሰ ሰነ ልቦና ስለሌለው ነው፡፡ ርዕዮትን የፈቷት በግፊት መሆንን ማመናቸው አንድ ነገር ሆኖ በህገወጥ ሁኔታ በእስር እንደነበረች ግን የምንረሳው አይደለም፡፡ (የፍርድ ቤቶች ውሳኔ ልክ ነው ቢባል እንኳን የእስር ጊዜ ጨርሳ አንፈታም ብለው አስረው ነበር ያስቀመጧት)፡፡

ጠቅላይ ሚኒሰትራችነ ነጋዴዎች እስር ቤት እንዳላቸው የነገሩን ነገር ብዙ የሚገርም አይደለም፡፡ በእኛ ሀገር ኤምባሲዎች እስር ቤት እንደነበራቸው ይውራ ነበር (ኤርትራ ኤምባሲ)፡፡ ይህ ግን የሚሆነው በመንግሰት የደህንነት ሰዎች ድጋፍና ትብብር ብቻ ነው ሊሆን የሚችለው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሁንም የትኛው ነጋዴ የት ቦታ እስር ቤት አደራጅቶ ከማን ጋር ይስራ እንደነበር በግልፅ በስም ሊገልፁልን በዚሁ ሁኔታም ክስ ተመስርቶ ማየት እንፈልጋል፡፡ (Name and Shame)፡፡ የነጋዴ ነገር ከተነሳ ነጋዴ በሙሉ ሌባ ነው ያሉትን ግን ትክክለኛ የንግድ ምክር ቤት ተወካይ ቢኖር ይቅርታ እንዲጠይቁ ማድረግ ነበረበት፡፡ ይህ ሁሉ ነጋዴ ግብር እየከፈለ ያቆማትን ሀገር ሁላችሁም ሌቦች ናችሁ ማሰር ብንፈልግ ማለት በፍፁም ልክ አይደለም፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትራችን አንድም ቀን በንግድ ተሳትፈው ስለማያውቅ ነጋዴዎች ትርፍ ለማሳደግ ሚወሰዷቸው እርምጃዎች በሙሉ የሌብነት ስራ ነው፡፡ ህጋዊ የሆነ የታክስ መቀነስ እንቅስቃሴ በትምህርት/በህውቀት (Legal Tax Evation) የተደገፈ መሆኑን የሚነግራቸው አማካሪ የላቸውም፡፡
አሁንም ዜጎችን ከሰላማዊ ትግል ወደ ትጥቅ ትግል እየገፋ ያለው መንግሰት መሆኑን፣ ሌባ ያሉትን ነጋዴ ይቅርታ መጠየቅ እንደሚገባ፣ እስር ቤት ያደራጁ ነጋዴዎች ካሉ በይፋ ለህዝብ ይፋ መደረግ ይኖርበታል፡፡