ጠቅላይ ሚኒሰትራችነ ነጋዴዎች እስር ቤት እንዳላቸው ነገሩን::እስር ቤት ያደራጁ ነጋዴዎች ካሉ በይፋ ለህዝብ ይፋ መደረግ ይኖርበታል፡፡
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
ጠቅላይ ሚኒሰትራችነ ነጋዴዎች እስር ቤት እንዳላቸው የነገሩን ነገር ብዙ የሚገርም አይደለም፡፡ በእኛ ሀገር ኤምባሲዎች እስር ቤት እንደነበራቸው ይውራ ነበር (ኤርትራ ኤምባሲ)፡፡ ይህ ግን የሚሆነው በመንግሰት የደህንነት ሰዎች ድጋፍና ትብብር ብቻ ነው ሊሆን የሚችለው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሁንም የትኛው ነጋዴ የት ቦታ እስር ቤት አደራጅቶ ከማን ጋር ይስራ እንደነበር በግልፅ በስም ሊገልፁልን በዚሁ ሁኔታም ክስ ተመስርቶ ማየት እንፈልጋል፡፡ (Name and Shame)፡፡ የነጋዴ ነገር ከተነሳ ነጋዴ በሙሉ ሌባ ነው ያሉትን ግን ትክክለኛ የንግድ ምክር ቤት ተወካይ ቢኖር ይቅርታ እንዲጠይቁ ማድረግ ነበረበት፡፡ ይህ ሁሉ ነጋዴ ግብር እየከፈለ ያቆማትን ሀገር ሁላችሁም ሌቦች ናችሁ ማሰር ብንፈልግ ማለት በፍፁም ልክ አይደለም፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትራችን አንድም ቀን በንግድ ተሳትፈው ስለማያውቅ ነጋዴዎች ትርፍ ለማሳደግ ሚወሰዷቸው እርምጃዎች በሙሉ የሌብነት ስራ ነው፡፡ ህጋዊ የሆነ የታክስ መቀነስ እንቅስቃሴ በትምህርት/በህውቀት (Legal Tax Evation) የተደገፈ መሆኑን የሚነግራቸው አማካሪ የላቸውም፡፡
አሁንም ዜጎችን ከሰላማዊ ትግል ወደ ትጥቅ ትግል እየገፋ ያለው መንግሰት መሆኑን፣ ሌባ ያሉትን ነጋዴ ይቅርታ መጠየቅ እንደሚገባ፣ እስር ቤት ያደራጁ ነጋዴዎች ካሉ በይፋ ለህዝብ ይፋ መደረግ ይኖርበታል፡፡