የሰማያዊ አባላትን ጨምሮ 13 ሰዎች የሽብር ክስ ተመሰረተባቸው


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


የሰማያዊ አባላትን ጨምሮ 13 ሰዎች የሽብር ክስ ተመሰረተባቸው

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን ጨምሮ 13 ሰዎች ዛሬ የካቲት 27/2008 ዓ.ም በፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡
በጋሞ ጎፋ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ አደራጅ በሆነው አቶ ሉሉ መሰለ ስም በተከፈተው የክስ መዝገብ የተካተቱት ተከሳሾች፡-
1. ሉሉ መሰለ
2. ዓለም ክንፈ
3. አየለች አበበ
4. በጋሻው ዱንጋ
5. በረከት ተገኔ
6. ደረጀ አደመ
7. ዘኪዮስ ዘሪሁን
8. ጌታሁን ቃጻ
9. ሲሳይ አምባው
10. መርዶኪዮስ ሽብሩ
11. መሀመድ ዳና
12. አጥናፉ አበራ፣ እና
13. ያረጋል ሙሉዓለም ናቸው፡፡

ተከሳሾች በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሸባሪ ተብሎ በተሰየመው አርበኞች ግንቦት ሰባት የሽብር ድርጅት ተግባር ውስጥ ለመሳተፍ አባል ሆነው ኤርትራ ባለ የድርጅቱ አባል ትዕዛዝ መሰረት በፈጸሙት በሽብርተኛ ድርጅት ውስጥ በማናቸውም መልኩ በመሳተፍ የጸረ-ሽብር አዋጁን አንቀጽ 7(1) ተላልፈዋል በሚል መከሰሳቸውን የአቃቤ ህግ ክስ ያስረዳል፡፡
ተከሳሾች ከአርባ ምንጭ ከተማ ወደ አዲስ አበባ እንዲመጡ ተደርገው ከዛሬ አራት ወራት ጀምሮ በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡