መንግስት የህዝበ ሙስሊሙን ኮሚቴዎችንና ቤተሰቦቻቸውን በቃሊቲ ማወከብ መቀጠሉ ታወቀ ።


መረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ


መንግስት ኮሚቴዎቻችንና ቤተሰቦቻቸውን በቃሊቲ ማወከብ መቀጠሉ ታወቀ ።

ሬዲዮ ዳንዲ ሀቃ ጥር 11 /2008

የህዝበ ሙስሊሙን የመብትጥያቄ : ይዘው መፍትሄ ለማፈላለግ በመንቀሳቀሳቸው ብቻ በአምባገነኑ ስርአት እጅ ወድቀውና : በመንግስታዊው የካንጋሮ ፍርድ ቤት ጥፋተኛ ተብለው : ከሰባት አመት እስከ ሀያ ሁለት አመት ተፈርዶባቸው : በየማጎሪያ ጣቢያው ታጉረው በሚገኙ የህዝበ ሙስሊሙ መሪዎች ላይ : አንባገነኑ ስርዓት እያደረሰባቸው ያለው ግፍ አሁንም መቀጠሉ ታወቀ ።ፖሊሱን ስሙን ቢጠይቁትም ስሙን ሊናገር ማን እንዳዘዘው ቢጠይቁትም ያዘዘውን አካል መናገር አልፈለገም ።

ኮሚቴዎቻችንም የሰው መብት ለመጣስ ከመነሳትህ በፊት ስለ መብት ልታውቅ ይገባል እያሉ መብቱን የማያውቅ ተላላኪ መሆኑን አስደረድተውታል ።

የኮሚቴዎቻችን ቤተሰቦች ከኮሚቴዎቻችን ጋር ሳይገናኙ ምግቡን ብቻ ሰጥተው መመለሳቸው ታውቋል ።

በተያያዘ ዜናም ባለፈው ሳምንት በቃሊቲ ማረሚያ ቤት የእስር ቤቱ ሃላፊዎች መልካም አስተዳደርን በሚመለከት እስረኞችን ሰብሰበው ባነጋገሩበት ወቅት : በእስር ቤቱ ሁሉ ነገር የተሟላ ይመስል ምን ችግር አለ ብለው ሲጠይቁ :ጀግኖች ኮሚቴዎቻችንም በእስር ቤቱ ምንም አይነት መልካም አስተዳደር የሚባል ነገር እንደሌለ መግለፃቸው ተውቋል ።

በስብሰባው ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት ኮሚቴዎቻችን መልካም አስተዳደር እንደሌለ ካስረዱባቸው መገለጫዎች መካከል ሌላው ቀርቶ በእስር ቤቱ ህገ መንግስቱ ያስቀመጠው ሁሉም ሃይማኖት እኩል ነው የሚለው እንደማይከበር ገልፀው ።

በእስር ቤቱ በቆዩባቸው አመታት ብዙ የሙስሊም አመታዊ በአላት ቢያልፋም እንደ ሌላው እምነት በዓላት አንድም ቀን ለሙስሊሙ እስረኛ በሬ ታርዶ አለማየታቸውን ገልፀዋል ።

ይህ ማለት ግን ለሌሎች እምነት ተከታዮች ለምን ተደረገ ማለታቸው እንዳልሆነ በግልፅ ቋንቋ ነግረዋቸዋል ።

ከዚህ በተጨማሪም ኮሚቴዎቻችን ሌሎች በእስር ቤቱ አየተፈፀሙ ያሉ ህገ ወጥ ተግባሮችን እያነሱ መልካም አስተዳደር የሚባለው ነገር በግቢው ውስጥ ፍፁም እንደሌለለ በግልፅ ቋንቋ አስቀምጠውላቸዋል ።

ኮሚቴዎቻችን በተገኘው አጋጣሚ የአምባገነኖችን ህገ ወጥ ስራ ማጋለጣቸውና ወኔያቸው እንዳለ መሆኑ እንቅልፍ የነሳቸው የአምባገነኑ ስርዓት ደህንነቶች በእነርሱ ላይ እያደረሱ ያሉትን በደል አጠናክረው ቀጥለዋል ።

ኮሚቴዎቻችን በግፈኞች እጅ ሆነው አሁንም አምባገነኖችን ይጋፈጣሉ አሁንም ለመብታቸው ይታገላሉ ።

እኛስ ትላንት ኮሚቴዎቻችንን መርጠን የላክናቸው ሙስሊሞች ምን እየሰራን ነው ?
ለትግሉስ ምን እያበረክትን ነው? እኛ ብንተኛም እነርሱ እንደማይተኙልን እያሳዩን ነውና : ሁላችንም ትግሉ ግቡን እንዲመታ የአቅማችንን እናበርክት ።

Ayda Fuad Ayda Fuad's photo.