አንዳንድ ፣ አሸባሪ ፣ ልማት እና ወዘተ፣ የቃላት ትርጉም ( ሄኖክ የሺጥላ )
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
አንዳንድ ፣ አሸባሪ ፣ ልማት እና ወዘተ፣ የቃላት ትርጉም ( ሄኖክ የሺጥላ )
አንድ ወዳጄ <አንዳንድ> የሚለው ቃል ትርጉም ምን ማለት እንደሆነ ልታስረዳኝ ትችላለህ ወይ ብሎ የቃላት እውቀቴን ተፈታተነው ። በመጀመሪያ በፈረንጅኛው a small amount or number of people or things የሚለው ሊሆን ይችል ይሆን አልኩ ? ሲገባኝ ግን <አንዳንድ> በ ( contextual meaning ) አገባብ ትርጉሙ ላይ መሰረት ያደረገ የቃላት ትርጉም ከሆነ ደሞ ሊለይ እንደሚችል ስለማውቅ ፣ አንዳድን ማለት አንዳንድ ጊዜ ብዙ ማለት ሲሆን አንዳንድ ጊዜ ደሞ ጥቂት ማለት ነው አልኩት ሳስረዳውም የሚከተለውን ምሳሌ ጠቀስኩ ።
አንዳንድ የሚለውን ቃል የሰማኸው በ ኢትዮጵያ ቴሌቭዥን እና ራዲዮ ከሆነ ፣ አንዳንድ ማለት እጅግ በጣም ብዙ ፣ ሊቆጠር የማይችል ፣ ህልቆ-መሳፍርት ፣ የትየ-ለሌ ፣ ወይም ( negative infinitive ) ወይም እንጦሮጦስ ማለት ሊሆን ይችላል ። ይህንን አንዳንድ የሰማኸው ሌላ ሀገር ከሆነ ትርጉም ( insignificant ) ( ይህን-ታህል ) ወይም ጥቂት ወይም ከቁጥር የማይገባ ማለት ነው ። ስለዚህ የቃላት ትርጉም ከቃሉ ምንነት ተነስተን ብቻ ትርጉም የምንሰጠው ነገር እንዳልሆነ ልንረዳ ይገባል ።
ለምሳሌ አሸባሪ ( terrorist ) የሚለውን ቃል ኢትዮጵያ ውስጥ ከሆነ የሰማኸ ፣ ትርጉሙ ጋዜጠኛ ፣ ጠሐፊ ፣ የመንግስትን አሰራር ተጠያፊ ። ሀይማኖተኛ እና ህገ መንግስቱን አክብሮ የሚኖር ሕዝብ ፣ ህገ መንግስቱን ረግጦ በሚኖር መንግስት የሚወጣለት ስም ማለት ሲሆን በሌሎች ሀገሮች ግን አሸባሪ ማለት ከጥሬ ትርጉሙ ሌላ የአገባብ ትርጉም የለውም ።
ለምሳሌ ልማት የሚለውን ቃል ብንወስድ ። ይህ ቃል በኢትዮጵያ በከፍተኛ ሁኔታ ተነግሮለት ግን ያን ያህል አድማጭ ያላገኘ ቃል ነው ። ምክንያቱ ደሞ < ልማት > የሚለው ቃል በሀገራችን ኢትዮጵያ ሲተረጎም የሚከተለውን ቀለም ስለሚይዝ ነው
ልማት ማለት ፣ ህወሓት ሲሰርቅ ሌላው ቆሞ የሚያይበት የኑሮ መስመር ነው ።
ልማት ማለት ፣ ያንድ ጎሳ አባላት ሀገሪቷን ሲመዘበሩ ሌሎች ዝም ይሉ ዘንድ የተነገራቸው ማግባቢያ ቃል ነው ።
ስለዚህ አንድ ኢትዮጵያዊ ልማት ላይ ነን እንስራበት ካለህ ፣ በ 11 ፐርሰንት አድጌ ፣ ምንም የምበላው የሌለበት ሀገር ሕዝብ አባል ነኝ ማለቱ ነው ። ታስጨርሰኛለህ እኔ ፖለቲካ አልፈልግም ማለቱ ነው ። ልማት ላይ ነን ማለት አጭር ትርጉሙ ፣ ፍርሃት ላይ ነን ፣ ዝምታ ላይ ነን ማለት ነው ። ስለዚህ ወዳጄ ቃል እንደ አገባቡ ነው የሚፈታው ።