ባህርዳር ከተማ ማረሚያ ቤት የሚገኙ እስረኞች የሚደርስባቸውን በደል በመቃወም ተቃውሞ አሰሙ
የመረጃ ቲቪ አባል በመሆን የሳተላይት ቲቪውን ቀጥታ ስርጭት፣ ወቅታዊ ዜናዎችን እና ትንተናዎችን፣ የመዝናኛ ፕሮግራሞችን፣ ስፖርት እና ሌሎችንም ዝግጅቶቻችንን በፍጥነት እና ጥራት ስልክዎ፣ ኮምፒዩተርዎ ወይም ቲቪዎ ላይ ማየት ይችላሉ። እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን አባል ይሁኑ።
የሚደርስባቸውን በደል በመቃወም ባህርዳር ላይ እስረኞች ተቃውሞ አሰሙ
#Ethiopia #BahrDar #Ethiopiaprotests #NegereEthiopia #MinilikSalsawi
ባህርዳር ከተማ ማረሚያ ቤት የሚገኙ እስረኞች የሚደርስባቸውን በደል በመቃወም ከትናንት ታህሳስ 9/2008 ዓ.ም ጀምሮ በእስር ቤቱ የሚዘጋጀውን ምግብ እንደማይበሉ ማሳወቃቸውንና ጩኸት በማሰማት ተቃውሟቸውን መግለፃቸውን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልፀዋል፡፡ በትናንትናው ዕለት በማረሚያ ቤቱ የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ያመልጣሉ በሚል በእግር ብረት ታስረው እንደሚገኙ መዘገባችን የሚታወስ ሲሆን እስረኞቹ በርካታ በደሎች እየደረሰባቸው እንደሚገኝ ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡
በተለይ በሽብር ሰበብ የታሰሩ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ከሚደርስባቸው ድብደባ ባሻገር ህክምና እንደማያገኙም ምንጮች ዘግበዋል፡፡ ከዚህ ባሻገር በእስር ቤቱ የሚቀርበው ምግብ ለበሽታ የሚያጋልጥ በመሆኑ ከትናንት ጀምሮ እስር ቤቱ የሚያቀርበውን ምግብ አንበላም ማለታቸውና የተቃውሞ ጩኸት ማሰማታቸውም ተገልፆአል፡፡
በባህርዳር ማረሚያ ቤት የሚገኙ እስረኞች ከትናንት ታህሳስ 9/2008 ዓ.ም ጀምሮ ተቃውሞ በማሰማታቸው በዛሬው ዕለት ቤተሰቦቻቸው እንዳይጠይቋቸው እንደተከለከሉም የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልፀዋል፡፡